#ምድር በራች ሚካኤል ሲመጣ# ___ ምድር በራች ሚካኤል ሲመጣ ገናና ነው አሰሙት እልልታ ሚካኤል /2/የአምላክ ባለሟል ___ ክንፉን ሲዘረጋ ውሀ ተናወጠ በክብር ሲገለጥ ነገር ተለወጠ በፍቅሩ ተዳሰው ድውያን ዘለሉ የሚካኤል አምላክ ይባረክ እያሉ አዝ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ብርሀን የሚተፉት ግሩማን አይኖቹ በፍቅር ያዩናል ዘውትር ሳይሰለቹ ሲቀድም ሲመራ ተከፍሏል ባህሩ ከርሱ ጋር የወጡ ሞትን ተሻገሩ አዝ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አለሁ ብዙ ዘመን ዝናህን ስሰማ በፋርስም አንተው ነህ በግብፅም ከተማ ወጥቼ አልቀረሁም ከአገር ተሰድጄ ዳግም አርፌአለሁ ባንተ በወዳጄ አዝ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። የዳቢሎስ ዙፋን ተገልብጧል በእርሱ ጠላት ሚደቅበት መብረቅ ነው ቀሚሱ ቆሟል ዙፋኑ ፊት ምህረት እየጠና ያደረገው ተአምር መቼ ተነካና አዝ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ክንፉን ሲዘረጋ ውሀ ተናወጠ በክብር ሲገለጥ ነገር ተለወጠ በፍቅሩ ተዳሰው ድውያን ዘለሉ የሚካኤል አምላክ ያባረክ እያሉ @maheberat @maheberat For any comment @Natnael1201 254 viewsNata , edited 07:03