አበበና ጫላ አጀንዳ ስታጣ ፣ በስም አትጣላ! አንተም ጩቤ ጨብጥ ፣ አንተም በሶ ብላ ጨቡዴ ሁን ሀጎስ ፣ አቶቴም ሁን ሺፋ ማንም ይበሉህ ማን ፣ ሲጠሩህ አትጥፋ አቤት በል በኩራት ፣ ክብርህን አትጣው መልአክ ቢሆንም ፣ ስምን የሚያወጣው እኛ ግን እኛ ነን ፣ ሀያል ያልበገረን አለማወቅ እንጂ ፣ የሚያከራክረን እንዳልተገዛን ነው ፣ ስማችን ሚነግረን። ።።። አሁን ለምሳሌ ምኒሊክ ተወልዶ ፣ ባይጠገን ቅስሜ ምኒልክ ተወልዶ ፣ ባይፈታ ህልሜ በላቶቪች ነበር ፣ በላይ ሚሉት ስሜ! ➤ከወደዱት በቅንነት ይቀላቀሉን! @liulzemaryam @liulzemaryam @liulzemaryam 3.9K views08:59