Get Mystery Box with random crypto!

ሐባን ኢብኑ ሙንቂዝ [ረዐ] እንደዘገቡት: «አንድ ሰውዬ እንዲህ አለ: ‐ «የአላህ መልክተኛ ሆ | Bilal Media & Communication

ሐባን ኢብኑ ሙንቂዝ [ረዐ] እንደዘገቡት:

«አንድ ሰውዬ እንዲህ አለ: ‐ «የአላህ መልክተኛ ሆይ! የዱዓዬን ሲሶ ለርሶ ሶለዋት ላድርገው?»
እርሳቸውም:‐ «ከፈለግክ አዎን!» አሉት።
«ሁለት ሶስተኛውን ላድርገው?» አላቸው።
«አዎን!» በማለት መለሱለት።
«ሁሉንም ለርሶ ሶለዋት ላድርገው?» ጠየቀ።
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ አሉ:‐ «እንደዚያ ከሆነ ያሳሰበህን የዱንያም ሆነ የአኺራን ነገር አላህ ይገላግልሀል።»
ሹዐቡል‐ኢማን ላይ በይሀቂይ ዘግበውታል።