Get Mystery Box with random crypto!

ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ ዳን 10:13 ➼የኃይላት አለቃ ነው ቅዱስ ሚካ | ኬልቅያስ

ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ ዳን 10:13

➼የኃይላት አለቃ ነው ቅዱስ ሚካኤል
➼የሞት ደብዳቤን የሚለውጥ ነው።
➼ከእሳት የሚያወጣ መልአክ ነው።
➼የእግዚአብሔርን ቅዱሳን የሚራዳ የቅዱሳን ወዳጅ ነው።
➼ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ሲወጡ መንገድ መሪያቸው ሚካኤል ነው።
➼ጠላትን የሚያሳፍር ትዕቢተኛን የሚጥል እርሱ የመላእክት አለቃቸው ነው ቅ/ ሚካኤል።
"
""""" እንኳን ለመልአኩ የክብር በአል አደረሳችሁ""""

ይህ ተራዳኢ መልአክ በዚህች ቀን እግዚአብሔርን በሚፈሩት ዙሪያ ሰፍሮ ያዳነበት በኃይሉም ጠላትን የጣለበት በአሉ ነውና ይህችን ቀን አክብሯት እንድትከብሩባት።

ይህም የፋርስ ንጉሥ ሰናክሬም ኢየሩሳሌምን በከበባት ጊዜ በእግዚአብሔርና በሕዝቅያስ ላይ በድፍረት ተናገረ። "" አሁን ከእጄ የሚያድናችሁ የለም"" አለ።
ንጉሡ ሕዝቅያስም እርሱንና ሕዝቡን ሊያድን በታመነ በእግዚአብሔር ፊት ማቅ ለብሶ አመድ ነስንሶ ጸለየ አለቀሰ። እግዚአብሔርም ቅ/ሚካኤልን ላከው። ሰናክሬም የተመካባቸውን 185 ሺ ሰራዊት በትዕቢቱ አጣ። ይህን ያህል ወታደር በሊቀ መላእክት እጅ ተቀጣ። ለዚህ ዛሬ የዳንኤልን ዝማሬ ሕዝቅያስ ዘመረው።
""" ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ"""

.እኔም ምልጃውን አውቀዋለው በችግሬ ቀድሞ የሚደርስልኝ ሚካኤል ረዳቴ ነው።
.ከመንገዱ እንዳልወጣ ቃሉን የመገበኝ ሚካኤል መምህሬ ነው።
.ስደክም የሚያበረታኝ መልአኩ ደጋፊዬ ነው።
.ስራብ የሚመግበኝ ሚካኤል መጋቢዬ ነው።
.ስደናቀፍ የያዘኝ ደግሞም የደገፈኝ ሚካኤል ረዳቴ ነው።
.ቅ/ሚካኤል የችግሬ ደራሽ አማላጄ ያሳደገኝ አባቴ ነው። ለእኔ ያላደረገው ምን አለ?"""" ለእኔ ያደረገው እጅግ ብዙ ነው።""
. ዛሬም በችግሬ ቀድሞ ደርሷልና እኔም እንደ አባቶቼ.....

ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ። የሚል ዝማሬ ከአንደበቴ ነው።

ምልጃው አይለየን አሜን ለዘለዓለም።
ሐምሌ 12-2014
* * ናትናኤል **