Get Mystery Box with random crypto!

በመጨረሻም ቅዱስ ሲኖዶስ በጀመረው ፍጹም ሰላማዊ ና ሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ጋር የደረስንበትን ው | ዘማሪ ክብሮም

በመጨረሻም ቅዱስ ሲኖዶስ በጀመረው ፍጹም ሰላማዊ ና ሕጋዊ መንገድ ከመንግሥት ጋር የደረስንበትን ውጤት በየጊዜው የምናሳውቃችሁ ስለሆነ እንደዚህ ቀደሙ ፍፁም በሆነ
መንፈሳዊ ጨዋነት የቅዱስ ሲኖዶስን መልእክት እንድትጠባበቁ፤ አሁንም ቢሆን ያለመዘናጋት ቤተ
ክርስቲያናችሁን በጥብቅ ሁኔታ እንድትጠብቁ እና ቤተ
ክርስቲያናችሁ ላይ የሚያጋጥሙትን ችግሮች ሁሉ በተዋረድ
ላለው መዋቅራችሁ እንድታሳውቁ አባታዊ መልእክታችንን
እናስተላልፋለን፡፡
ያዕቆብ መልእክት ፩፤፪-፫ “ወንድሞቼ ሆይ የእምነታችሁ
መፈተን ትእግስትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፤ ልዩ ልዩ
ፈተና ሲደርስባችሁ እንደሙሉ ደስታ ቁጠሩት”
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ
የካቲት ፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ