Get Mystery Box with random crypto!

ኬብሮን “እናንተ እምነት የጎደላችሁ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ” (የብጹዕ አቡነ ሽኖዳ አባታዊ ምክር) | ✞ኬብሮን

ኬብሮን

“እናንተ እምነት የጎደላችሁ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ”
(የብጹዕ አቡነ ሽኖዳ አባታዊ ምክር)
እኛ ከእግዚአብሔር እድንርቅ ካደረጉን ነገሮች አንደኛው ጭንቀት ነው ። ጭንቀት
ማለት ስለተከሰቱና ይከሰታሉ ተብለው ስለሚታሰቡ መንፈሳዊ እና ሥጋዊ
ጉዳዮች አብዝቶ በማሰብ በስጋት ተውጦ መረበሽ ማለት ነው። ዓለም በብዙ
አስጭናቂ ጉዳዮች በመሞላቷና ሰውም የሚኖረው ዓለም ላይ እንደመሆኑ
አብዛኛው ሰው ሊጨነቅ ይችላል። “ጭንቀትን የተመላ ይህ ዓለም ያልፍ ዘንድ
ይቸኩላል” ዕዝ.ሱቱ 2፥27 እንዳለ ዕዝራ። ኦክስፎርድ ጭንቀት የሚለውን
ሲተረጉመው " ከቁሣዊ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት
ይለዋል " የተሻለው ትርጉሙ ግን አላስፈላጊ ነገሮችን ከመፈለግ የተነሣ
የአእምሮ ወይም የስሜት ድካም ፤ ውጥረት ፤ ወይም ሕመም ማለት ነው ።
ጭንቀት ለሕይወታችን ከምንፈልጋቸው ወይም አላስፈላጊ
ከሆኑ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ነው ። ስለሆነም
የጭንቀት መንስኤው ምንድን ነው ? ስንል # ተስፈኝነት ሆኖ እናገኝዋለን ።
በአጠገባችን ካሉ ሰዎች ቃል ከገቡልን ፤ ከሚቀርቡን ፤ ከቤተሰቦቻችን ወዘተ
የምንጠብቀው አለ ። ተስፈኝነት በሁለት መንገዶች ሊመጣ
ይችላል ። የመጀመሪያው ስለ ሰዎች ያለን ተስፈኝነት አለ ። ሌላውኛው ሰዎች
ስለ እኛ አላቸው ብለን የምናስበው ነው ።
በማንኛውም መንገድ የተጨነቀ ሰው ከገጠማችሁ ከሁለቱ በአንዱ ምክንያት
እነደሆነ ታረጋግጣላችሁ ። ሌላ ሰው ለእኛ ዝቅተኛ ግምት ሠጥቶን ሊሆን
ይችላል ። ወይም እኛ
ራሳችንን ዝቅ አድርገነው ሊሆን ይችላል ። ወይም እግዚአብሔር እንደተወን
አድርገን ልንወስድ እንችላለን ። ወይም ከእግዚአብሔር እንደራቅን ሊሠማን
ይችላል ። ጭንቀት ከእነዚህ የአንዱ ስሜት ውጤት ነው ። የቁስ እቃ ፍላጎት
እንድንጨነቅ ያደርጋል ። ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም አንዳንድ ጊዜ
አወንታዊ በሆነ መልኩ ለስሜቱ ምላሽ እንሰጣለን ። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ
አሉታዊ መልስ እንሰጣለን ። ሌላ ጊዜ ደግሞ አወንታዊም አሉታዊም ሳይሆን
ይቀራል ።
ከጭንቀት ለመላቀቅ የሚረዳ ዋነኛው ዘዴ ተፈጥሮአዊ ማንነታችንን ማሰብ ነው
። ቁሣዊ ሆነን
አልተፈጠርንም ። የተፈጠርነው በእግዚአብሔር አርአያ እና አምሳል ነው ።
መቅደሱ ሆነን ነው የተፈጠርነው ።
ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር ነው የተፈጠርነው ። ግፊቱም ፤ ጭንቀቱም
፤ሕመሙና ፤ውጥረቱ ፤ በመጣ ጊዜ ለእግዚአብሔር አሳልፈን መስጠት
ይኖርብናል ። ከእግዚአብሔር ኃይል በላይ የሆነ ግፊት ወይም ውጥረት የለም ።
ስለሆነም እኔ ተሸክሜ ከምጨነቅ እግዚአብሔር እኔን ሆኖ እንዲሸከም
አደርጋለሁ ። እርሱ ጫናወቻችንን ያቀላል ።
ዮሴፍ በብዙ ጫናወች ውሰጥ ይኖር ነበር ። ወድሞቹ ጉድጓድ ላይ ሲጥሉት
ምናልባት መረዳት በማይችልበት በሕፃንነቱ ጊዜ ነበረ ። እንደገናም ለባርነት
ሸጡት ። ከቤተሰቡም ጋር ተለይቶ መኖር ጀመረ ። የንጉሱ የፈርኦን ሚስት
በሐሰት ከሰሰችው ። በዚህም የተነሳ እስር ቤት ተጣለ። በእስር ቤት እያለ
ማንም የሚያስታውሰው አልነበረም ። ይህ እንግዲህ መጠነ ሰፊ ወደ ሆነ ጫና
ውስጥ ያመጣዋል ። ሆኖም ግን ዮሴፍ እነዴት ለመፍታት ሞከረ ? ችግሩን
እነዴት ተቋቋመው ? በእያንዳንዱ ሁኔታ ዮሴፍ ራሱ ዮሴፍ ነበረ ።
አልተለወጠም ። በሁሉምሁኔታዎች ተመሣሣይ ፤ ማንነት ፤ ፍቅር ፤ እምነት ፤
ነበረው ። እግዚአብሔርን አዘውትሮ ይጠራ እና ይለምን ነበረ ። እግዚአብሔርም
ሁል ጊዜ አጠገቡ ነበረ ።
ቦኑ እንከ ኢይከውነነ ናብእ መሥዋዕተ ስብሐት በኩሉ ጊዜ ለእግዚአብሔር ፍሬ
ከናፍሪነ ከመ ነእመን በስሙ
‹‹እንግዲህ ዘወትር ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት፥ ማለት ለስሙ
የሚመሰክሩ የከንፈሮችን ፍሬ፥ ለእርሱ እናቅርብለት።›› ዕብ 13፡15

share ydrg
@kebbron
@kebbron