2019-11-26 21:05:16
በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማሩ ሂደት ተጀምሯል
On Nov 26, 2019
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 16 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ተፈጥሮ ከነበረው ችግር ጋር በተያያዘ ተቋርጦ የነበረው የመማር ማስተማር ሂደት መጀመሩን የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስረስ ንጉስ ተናገሩ።
ከአካባቢው ማህበረሰብ፣ የሃይማኖት መሪዎች እና ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት ጋር በመነጋገር የተፈጠረውን አለመረጋጋት ለመቅረፍ የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውንም ነው የተናገሩት።
ከዚህ ባለፈም በተማሪዎች መካከል የዕርቀ ሰላም መርሃ ግብር በማካሄድ ችግሩን መቅረፍ መቻሉን ጠቅሰው፥ አሁን ላይ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው መመለሳቸውን አንስተዋል።
ዶክተር አስረስ እንዳሉት እስከ ትናንት ድረስ ግቢውን ለቀው የወጡ ተማሪዎች እንዲመለሱ በተደረገው ጥሪ መሰረት ወደ 8 ሺህ ተማሪዎች ተመልሰው በትምህርት ገበታቸው ላይ ተገኝተዋል።
ተፈጥሮ ከነበረው ችግር ጋር በተያያዘ ተማሪዎች የጠፉ የመማሪያ ቁሳቁሶችን ዩኒቨርሲቲው እንዲያሟላላቸው በጠየቁት መሰረት፥ ዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።
ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘም 11 ሰዎች ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በህግ እየታየ ነው ብለዋል።
ተማሪዎችና ወላጆችም በማህበራዊ የትስስር ገጾች የሚራገቡ የሃሰት መረጃዎችን በመተው እንዲረጋጉም ጥሪ አቅርበዋል።
አሁን ላይ ግቢውን ሙሉ በሙሉ ወደ ቀደመ ሰላሙ ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
አስተያየታቸውን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የሰጡ ተማሪዎች በበኩላቸው፥ ተፈጥሮ የነበረውን ችግር በማውገዝ አሁን ላይ ተረጋግተው እየተማሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ችግር ሲፈጠር በመነጋገር መፍታት ይገባል ያሉት ተማሪዎቹ፥ የቀሩ ተማሪዎች
17.1K viewsedited 18:05