Get Mystery Box with random crypto!

JUSTIN APOLOGETICS721]

የቴሌግራም ቻናል አርማ justin_apologetics721 — JUSTIN APOLOGETICS721] J
የቴሌግራም ቻናል አርማ justin_apologetics721 — JUSTIN APOLOGETICS721]
የሰርጥ አድራሻ: @justin_apologetics721
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 996
የሰርጥ መግለጫ

ከእስልምናና ከሌሎች ቤተ እምነቶች ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ መስጫ
“ #አንድ ጌታ #አንድ ሃይማኖት #አንዲት ጥምቀት፤”
— ኤፌሶን 4፥5
አስተያየት ካሎት @Againest_hereticss_bot ላይ ያድርሱን

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-09 17:04:40

213 views14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-09 13:00:42 በፍጥረት እሑድ ቀን ምን ተደረገልኝ? ሊቀ መምህራን መምህር ዘበነ ለማ https://t.me/Tmhrte_Tewahdo
219 views10:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-31 08:52:51
አሁን ደግሞ ፊታችንን ወደ ደብረ ታቦር መድኃኔዓለም የትርጓሜ መጻሕፍት ጉባኤ ቤት እናዞራለን::

ለፍልሰታ ቁርስ በጣም በትንሹ 150 ብር ብናወጣ ለአሥራ አምስት ቀኑ አስልተን ብናዋጣ ለቤተ ክርስቲያን የነገ ሕልውና እጅግ ወሳኝ የሆነውን ጉባኤ ቤት እንገነባለን::

2ኛ ነገ.6:1:- እነሆ፥ በፊትህ የምንቀመጥበት ስፍራ ጠብቦናል አሉት::

የባንክ ቁጥሩን ከዚህ ኮፒ አድርጉ:: ከቻላችሁ ያስገባችሁበትን ስሊፕ ወይም ስክሪን ሾት ኮሜንት ላይ አጋሩን:: ሌላውንም እንዲያነሣሣ ነው እንጂ የተማሪ ጸሎት ገና ይከተላችኁዋል::

1000278305701
311 views05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-31 08:43:09 የቱ ይሻላል..??

ገዳይ የሆነ
#አክራሪ_ሙስሊም
ወይስ
መጽሐፍ ቅዱስን የያዘ
#ፕሮቴስታንት

@Apostolic_Answers
240 views05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 15:05:09 ወንጌል ከመስማትና ከማንበብ ምን አዘገየን ምንስ አደከመን

እግዚአብሔር ደሙን አፍስሶ ነጻ አወጣን
ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛ በቀላሉ ልናየው የማይገባ እጅግ ትልቅ ነገር ነው ታዲያ ክርስቶስ ይህን በዋጋ የማይተመን እና በዋጋ የማይገለጽ እጅጉን ከባድ ውለታ ሰጥቶናል፡፡

እኛስ ምን ያክል
ተገንዝበናል
ጌታችን በምንም አይደለም የገዛን በደሙ ነው!
ከሲኦል ነጻ ወጥተናል ከባርነት ነጻ ወጥተናል እንደ ሀጢያተኛ ስንቆጠር የነበረበት ዘመን አልፏል መጋረጃው የጥል ግድግዳ በእርግጥ ፈርሷል ታዲያ እኛ በዘመነ ሐዋርያት ጊዜ አባቶቻችን ሐዋርያት የጻፉልን ወንጌል ይህንን ነገር በጉልህ ያስረዳናል ነገር ግን እግዚአብሔር ለብሉይ ኪዳን ሰወች ኦሪቱን በነቢያቱ እጅ አጽፍ በዘመነ ሐዲስ ደሞ ትምህርተ ወንጌልን ካስተማረ ቡሃላ ሐዋርያት ትምህርተ ወንጌልን ሰብከው አስተምረው ወንጌልን ጽፈዋል
እኛ ክርስቶስን የምንረዳበት የድህነታችን(የመዳናችን) ዜና የሆነውን ወንጌል ቅዱስ ወንጌል ጌታችን እጃቸው ውስጥ አስገብቷል ጽፈውታልም፡ማር(16:8).
እኛ ይህነን ወንጌል አንብበን የምናገኘው በረከት በራሱ ብጹዓን ያስብለናል ራዕይ(1:3).
ሌላው አይደለም የሚያነበው ብቻ እራሱ ብጹዕ ይባላል በማለት ቅዱስ ዮሐንስ ይነግረናል፡
ወንጌልን በማንበብ እራሳችን በዋጋ የተገዛን መሆናችንን በጥሞና እንረዳ ነገር ግን እኛ ወንጌልን ከመማር ይልቅ ወንጌልን ከማንበብ ይልቅ የልብ ወለድ እና የፈጠራ ተራ ወሬና ተረት አዘል መጽሐፍ በየ ገበያው በየሱቁ በየትራንስፖርቱ እየገዛን ቅንጭላታችንን ስንበርዝ እንውላለን የሚገርመው እነዚህ መጽሐፍቶች ከነ ደራሲው ሳይቀር የከሌ መጽሐፍ ሁለተኛው አልያም ሶስተኛው ህትመት አልወጣምወይ በማለት ይጠይቃል፡፡ በነገራችን ላይ ይህ ሰው የሐዋርያት ስራ የሚባለውን መጽሐፍ ማን ጻፈው ብሎ አያቅም አንዳንዴም የሐዋርያት ስራ የሚባል መጽሐፍ መኖሩንም ከነ አካቴው አያውቅም፡፡
ነገር ግን የአለም ፈላስፋ የጻፉትን ተረት አንዳንዴም ከሐይማኖት የሚያስወጡትን እርኩሳን መጽሐፍ ለማንበብ አይታክትም የህይወት መሪ የሆነውን ቅዱስ ወንጌል ለማንበብ ይታክታል ወይ ከነ ጭራሹ ፍላጎቱ የተዘጋም አይጠፋም፡፡
ይሕ ነገር የሚመነጨው ከስንፍና እና እያወኩ ሐጢያት ከማደርግ ሳላውቅ ይሻለኛል በማለት የራሱን የቅድመ ሁኔታ እና ሐሳብ ያራምዳል፡፡
በነገራችን ላይ ለማወቅ(ለማንበብ) ፍቃደኛ ባለመሆን እራሱ ሐጢአታችን መሆኑ ተቀምጧል ሮሜ( 1:28).
የህይወት መጽሐፍ ቅዱስ ወንጌልን መማር ማንበብ በረከት እንጅ አለማንበብ እና ለማወቅ ባለመውደድ የሚገኝ ጥቅም የለም፡፡
ቅዱስ ወንጌል የህይወት ቃል እንጅ ሌላ አላማ የለውም ባለማወቅም የሚደረግ ስህተት ከስህተት ይቆጠራልጂ ከስህተት ሐጢአት እና ከመከሰስ አያድንም እንደውም ለማወቅ ባልወደዱት ላይ ቅጣት አለው ሮሜ1:28
አላዋቂነትም ከተጠያቂነት አያስመልጥም ምሳ1:22
ስለዚህ የእግዚአብሔር ወንጌል ሕይወት የሚያድን መንፈስ የሚየድስ ከእግዚአብሔር ሕብረት የሚመጣ ሰይጣንን የሚያቃጥል ጠላት የሚያሳፍር ከክህደትም የሚያስመልጥ የተበላሸ ሕይወትን ወደ ንስሃ የሚያደርስ አንደበተ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል እስትንፋሰ መንፈስ ቅዱስ የሆነ ቅዱስ ወንጌል ነው ስለዚህ ይህንን ወንጌል በማንበብ ሕይወትን ከተያዝንበት ነገር ነጻ እናውጣ ምክንያቱም ሰው ለተሸነፈበት ነገር ባሪያ ነውና (ቅዱስ ጴጥሮስ(2ኛጴጥ(2:19))).
ያሸነፈን ሱስ ከሆነ የሱስ ባሪያ ነን
ያሸነፈን ዝሙት ከሆነ የዝሙት ባሪያ
ያሸነፈን ክህደት ከሆነ የክህደት ባሪያ
.
.
.
ስለዚህ ለሐጢያት ባሪያ ከምንሆን ለክርስቶስ ልጆች ብንሆንስ?
ልጆች ከሆንን ደሞ ልጅ ያባቱን ይወርሳል (ቅዱስ ጳውሎስ(ሮሜ(8:17))).


https://t.me/Tmhrte_Tewahdo
253 views12:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 14:35:34
“..ሰይጣን በአንዳንዶች መስቀሉን ይክዱ ዘንድ በእነርሱ ላይ ሥራውን ይሠራል፣ የጌታችንን ሕማማቱንና ሞቱን እንዲያፍሩበትና ምትሐት ነው እንዲሉ በውስጣቸው ይሠራባቸዋል፣ ከድንግል መወለዱንና ሥጋ መልበሱን፣ እንዲሁም የእኛን ባሕርይ ርኩስ እንደ ሆነ አድርጎ ይነቅፋል። ከአይሁድ ጋር ደግሞ ሰዎች መስቀሉን እንዲክዱ ቤተ ክርስቲያንን ይዋጋታል፣ ከአሕዛብ ጋር ደግሞ ድንግል ማርያምን ይነቅፋሉ ያክፋፈላሉ፣ ክርስቶስ ከእርሷ ባሕርይዋን ገንዘቡ አድርጎ እንዳልተወለደ አድርገው ይናገራሉ። የክፋት ሁሉ መሪና ፍታውራሪ የሆነው ዲያብሎስ አሠራሩ ብዙ ዓይነት ነውና፣ እርሱ የሰዎች ፈታኝና አታላይ እንደ መሆኑ ሰዎችን በተለያዩ መንገዶች ከእውነት ይለያቸው ዘንድ ይፈትናቸዋል..።”

ቅዱስ አግናጥዮስ
The Epistle of Ignatius to the Philippians : chapter: [The malignity and folly of Satan. ]

ከብዙ ጊዜ መጥፋት በኋላ ተመልሰናል።

ሰላም ለናንተ ይሁን ብለናል።
334 viewsedited  11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 14:28:39
328 views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 08:09:57
342 views05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 19:20:44 ምሳሌ 30
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ ሁለትን ነገር ከአንተ እሻለሁ፥ ሳልሞትም አትከልክለኝ፤
⁸ ከንቱነትንና ሐሰተኛነትን ከእኔ አርቃቸው፤ ድህነትንና ባለጠግነትን አትስጠኝ፤ ነገር ግን የሚያስፈልገኝን እንጀራ ስጠኝ፥
⁹ እንዳልጠግብ እንዳልክድህም፦ እግዚአብሔርስ ማን ነው? እንዳልል፤ ድሀም እንዳልሆን እንዳልሰርቅም፥ በአምላኬም ስም በሐሰት እንዳልምል።
470 views16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 09:25:15
“ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ መሆኗን የማያምን ሰው ካለ ከእግዚአብሔር የተለየ ነው። ... ትስብእት መጀመሪያ ተፈጥሮ ከዚያ በኋላ የእግዚአብሔር ቃል አደረበት የሚል ቢኖር እርሱም የተወገዘ ነው።”

ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ
422 viewsedited  06:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ