ወደ ትግራይ የሚደረገው የሰብአዊ እርዳታ ጉዞ መቆሙን የተመድ አስታወቀ የተባበሩት መንግስት ድርጅት (ተመድ) የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ እንዳስታወቀው በየብስ እና በአየር ወደ ትግራይ ሲደረግ የቀየው የሰብአዊ እርዳታ ጉዞ መቆሙን አስታውቋ። በየብስ የሰብአዊ እርዳታ ከባለፈው ሀሙስ ጀምሮ የቆመ ሲሆን በአየር የሚደረገው እርዳታ ደግሞ አርብ ጀምሮ መቆሙን ቢሮ ገልጿል። ቢሮው እንቅስቃሴ በመቆሙ ምክንያት የእርዳታ ሰራተኞችን እንቅስቃሴ አስተጓጊሏል ብሏል። አስቸኳይ ተኩስ አቁም እንዲደረግ የጠየቀው ቢሮው የጸጥታው ሁኔታ የሚፈቅድ ከሆነ ቢሮው ከአጋሮቹ ጋር በመሆን ለተጎዱ ሰዎች እርዳታ እንደሚያቀርብ መግለፁን ዐልአይን ዘግቧል ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የሁሌ አዲስ ሚዲያ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ። Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/ Telegram : https://t.me/Hulaadiss YouTube Channel https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media 338 viewsEyasu Zekarias1, 15:04