Get Mystery Box with random crypto!

ቢመርህም ዋጠው =============== ①) የጎንደር ሙስሊሞች በአክራሪ ኦርቶዶክሶችና አሸባሪ | BOON TECH

ቢመርህም ዋጠው
===============
①) የጎንደር ሙስሊሞች በአክራሪ ኦርቶዶክሶችና አሸባሪ የታጠቁ ፋኖ ነን ባይዎች ክፉኛ ሲጨፈጨፉ ዝም ብሎ፤ ዝም ከማለትም አልፎ «አማራ ክልል ስለሆነ ነው!» እያለ በዘግናኝ ሁኔታ ተገድለው ሬሳቸው በመንገድ ላይ ሲጎተት ከተገደሉት ሙስሊሞች ይልቅ የክልሉ ስም በልጦበት ለገዳይ ጥብቅና የቆመ ሁሉ አሁን ወለጋ ላይ በአሸባሪው ኦነግ ሸኔ የተፈጸመውን ግፍ የማውገዝ ሞራል የለውም።

እዛው እጉያህ ውስጥ ያሉት የጎንደር ሙስሊሞች ሲገደሉ «አማራነታቸው» ያልታዬህን ወለጋ ላይ የወሎ ሙስሊሞች ሲገደሉ «አማራ ስለሆኑ ነው» የማለት ሞራል የለህም። ምክንያቱም የእውነት ለአማራነት የምትቆረቆር ቢሆን'ማ፤ ጎንደር ላይ በራሱ አማራ ነኝ በሚለው ጽንፈኛ ቡድን ለተገደሉትና በኦሮሚያ ልዩ ዞን የምኒልክ አፍቃሪዎች ከመኪና እያወረዱ ለገደሏቸው የአማራ ክልል ዜጎች ታዝንና ድምፅ ትሆናቸው ነበር። አንተ ግን ድምፅ መሆንህ ቀርቶ ጭራሽ ድምፅ የሆናቸውንም «አማራ ላይ ሲሆን ይጋነናል!» እያልክ ለማድበስበስ ትሞክር ነበር።
የባለዚሁ ሰው አሁን በወለጋ የተገደሉትን «አማራ ስለሆኑ ነው» እንዳትል። አስመሳይ!
*
②) በአማራ ክልል የጎንደር ሙስሊሞች በመስቀል ጦረኞች ሲጨፈጨፉና በወሎ ኦሮሞ ሙስሊሞች «ኦነግ ናችሁ» ተብለው በምኒልክ አፍቃሪዎች ሲጨፈጨፉ ተቃውመህ፤ አሁን ወለጋ ላይ ኦሮሞኛ ተናጋሪው ኦነግ ሸኔ የወሎ ሙስሊሞችንና ሌሎች ንጹሐንን ሲጨፈጭፍ ዝም ካልክ ወይም ሌላ ዘዴ ከፈለግክ ወይም «እና አማራ ክልል ላይ ሙስሊሙ ሲጨፈጨፍ የት ነበራችሁ?» ካልክ አንተ ኡስታዝም ሁን ባለስልጣን ድብን ያልክ አስመሳይ ሌባ ነህ። አሁን የወለጋውን ካለባበስክ፣ አጥፊውን በግልፅ ማውገዝ ሲገባህ ጭራሽ የሚያወግዙትን በተለያዩ ዘዴዎች ለማሸማቀቅና ለመወንጀል ከሞከርክ፣ በአማራ ክልል ሙስሊሞች ላይ የተፈጸሙትን ግፎች ያወግዝከው ለሙስሊሞች ተቆርቁረህ ሳይሆን የአማራ ጥላቻ ስላለብህ ነው።


የእውነት ለሙስሊሞች ተቆርቋሪ ብትሆን'ማ፤
እዛም እዚህም የተገደለው ሙስሊም ስለሆነ የገዳዩ ብሄርና ቋንቋ ማንም ይሁን ማንም ታወግዝ ነበር። እኔ የጎንደር ነፍሰ በላዎችን ሳወግዝ ቋንቋቸው አማርኛ መሆኑና ክልላቸው አማራ መሆኑ አላገደኝም። ከተበዳይ ጎን እንዲቆም እስልምናዬ አዞኛል። አንተም የወለጋ ነፍሰ በላዎችን ለማውገዝ ቋንቋቸው ኦሮምኛ መሆኑና ክልላቸው ኦሮሚያ መሆኑ ሊያግድህ አይገባም።


ከዚህ ውጭ ግን ይህቺን ተገን አድርገው ከጎንደሩ ጭፍጨፋ ጋር በማያያዝ ነገሩን ለማቃለል የሚሞክሩ አካላት አደብ ይያዙ። የጎንደር ሙስሊሞች የተገደሉበት ብቸኛ ምክንያት ሙስሊም መሆናቸው ነው። የወለጋ ወገኖቻችን ግን የተገደሉበት ምክንያት ከሙስሊምነት ባሻገር ከአማራ ክልል በተለይም ከወሎ የተገኙ መሆናቸው ነው። ስለዚህ ነጥለን እናውግዝ እንጂ ትይዩ አድርግን ማነጻጸር አይገባንም። አንዱን ሳያወግዝ ሌላውን የማውገዝ ማንም ሞራል የለውም። አፍህን ዘግተህ ታዘብ።


||
t.me/MuradTadesse