Get Mystery Box with random crypto!

ሰኔ 28/2014 ዓ.ም በጉመር ወረዳ በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች የ8ኛ ክፍል አቀፍ ብሔራዊ ፈተና | የጉመር ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት

ሰኔ 28/2014 ዓ.ም

በጉመር ወረዳ በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች የ8ኛ ክፍል አቀፍ ብሔራዊ ፈተና መሰጠት ተጀመረ።

የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በ23 የመፈተኛ ጣቢያ 2 ሺህ 507 ተማሪዎች ክልል አቀፍ ፈተና እየወሰዱ ይገኛል።

የጉመር ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት የፈተና ዝግጅት አስተዳደር የትምህርት ምዘና ጥናት ስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ አበበ ክንፈ እንደገለፁት ፈተናው ለመውሰድ ከተመዘገቡት 2 ሺህ 515 ተማሪዎች ውስጥ 7 ተማሪዎች ከመደበኛ እንዲሁም አንድ ተማሪ ከግል በጥቅልሉ 8 ተማሪዎች ለፈተናው አልተቀመጡም ብለዋል።

23 የጣቢያ ሃላፊዎች÷19 ሱፐርሻይዘሮች÷ 102 ፈታኝ መምህራን ፈተናውን ለመፈተን መመደባቸው አቶ አበበ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ለሁሉም ትምህርት ቤቶች ፖሊስና ሚሊሻ መመደቡንም ተናግረዋል።

በወረዳው 21 የመንግስት ትምህርት ቤቶችና 2 የግል ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 2 ሺህ 507 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና እየወሰዱ እንደሆነም ነው የገለፁት።

በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ያለምንም የጸጥታ ችግር እየወሰዱ እንደሚገኝም የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች ገልጸዋል ሲል የዘገበው የጉመር ወረዳ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

- ኢትዮጵያን እናልማ!
- የፈረሰውን እንገንባ!
- ለፈተና እንዘጋጅ!!

https://www.facebook.com/100068870753847/posts/pfbid0cRet6WifwTYAaGqP8X1HmPPJ19aNx1N55ev9tTZ8XFGPFcwAtR8jEdqEyDjxs751l/?app=fbl