Get Mystery Box with random crypto!

ከመፅሀፍት| from Books💚💛❤️

የቴሌግራም ቻናል አርማ frombooks1234 — ከመፅሀፍት| from Books💚💛❤️
የቴሌግራም ቻናል አርማ frombooks1234 — ከመፅሀፍት| from Books💚💛❤️
የሰርጥ አድራሻ: @frombooks1234
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.03K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩╩═╝
በቻናላችን ላይ
➠ አስገራሚ አስተማሪ እንዲሁም አዝናኝ ታሪኮችን
➠ የፍልስፍና ፅሁፎችን
➠ Motivation Quotes
➠ መፅሀፍትን በPDF
➠ ግጥም ያገኙበታል።
°
°
°
°
4 any comments and promotion (above 3k) @ktfi7

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-06 06:20:24 ኪነታዊ ውድድር፪፦ በኪነት ዘዮዳኒ

ውድድሩ በአጠቃላይ የኪነት ዘርፍ ማለትም፦

በአጭር ልቦለድ

በግጥም

)በድምጽ(በከቨር ሙዚቃ)

በወግ

በትወና ብቃት(ከ2 ደቂቃ ያልበለጠ ቪዲዮ)

በስእል

በኮሜዲ ቀልዶች እንዲሁም

በፎቶ ማንሳት(የሰው፣ የተፈጥሮ፣ እና የአሁናዊ ሁኔታ ፎቶዎች ማንሳት) የሚደረግ ሲሆን፤ ተወዳዳሪዎች ከተዘረዘሩት የውድድር ዘርፍ አንዱን በመምረጥ መወዳደሪያ ይዘታቸውን በ @znetsebrak
እና @ShewaWello እስከ ቀን ሰኔ 10/ 10ኛ ወር 2014ዓ.ም መላክ ይችላሉ።

የውድድሩ ህግ፦
1ኛ ተወዳዳሪዎች የሚልኩት መወዳደሪያ የራሳቸው መሆን አለበት።
ሲልኩ ከነ ሙሉ ስም አልያም የብእር ስምና ስልክቁጥር ጋር የተያያዘ መሆን አለበት!
2ኛ ውድድሩ ከተጀመረበት እለት ጀምሮ እስከ ፍፃሜው ተወዳዳሪዎች የሚለዩት በቻናሉ በተሰየሙ ዳኞች ብቻ ነው!
3ኛ ከ1ኛው ዙር ያለፉ 10 ተወዳዳሪዎች በቀጣዩ ወደ 5ቱ ውስጥ ለመግባት ይወዳደራሉ በስተመጨረሻም የፍጻሜ ውድድር ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለመውጣት ይፋለማሉ።

በውድድሩ፦
ኛ ለወጣ ምንትዋብ ታሪካዊ ልቦለድ
ኛ ለወጣ የደራሲ ናሁሰናይ ጸዳሉ ቴሎስ መጽሀፍ
ለወጣ የደራሲ ይስማዕከ ወርቁ ዛምራ መጽሐፍ

ማሳሰቢያ!!! ሽልማቱ የሚደርሳቹህ በsoftcopy (pdf format) ሲሆን መጽሐፍቶቹ እስከአሁኗ ሰአት በየትኛውም ቻናል ያልተለቀቁ አዳዲስ ናቸው
መልካም እድል

ቀ ላ ል➘➘➘
@gbw_dan


♡ ㅤ   ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
1.1K viewsዳኒ, 03:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 17:51:16 ፍቅር ቀዝቅዛለች ኮምቦልቻና ደሴ፣ ከከሚሴም ቢሆን የለንም መዋደድ:
የሰማዩ ጌታ ከመንበርህ ሳትወርድ፣ ወልድ እያ የኛን ጉድ።

24.09.014 (1:25ም)

me. ዮዳኤ

@frombooks1234
꧁༻༒༺꧂ ‌‌
1.5K viewsዳኒ, 14:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 17:13:08 ኪነት በዮዳኒ በአዲስ ነገር መጧል...

ድርሰት ለምትሞክሩ ለዚህ ቻናል አባላት አንዳንዴ ብልጭ የሚልልኝ "#የድርሰት_መነሻ_ሃሳብ" እንካቹህ ብያለሁ....በመነሻ ሃሳቡ በመንተራስ ራሳቹህ አስፋፍታቹህና የራሳቹህን ገፀባህርያት በመጨመር ወጥ ድርሰት እንድትፅፉ በቻልሁት መጠን የራሴን ልቁጥ አሻራ እነሆ.....



በትዕይንቱ መጀመሪያ ላይ አንድ የሰከረ ሰው ከውጭ ወደውስጥ ይገባል። ከውስጥ (ከመጋረጃው ጀርባ ሚስቱ አለች።)

ሰካራሙ፦ (እየተንገዳገደ ይገባና....የጎጇቸውን መሃል ላይ የምትገኘውን ምሰሶ ለመያዝ ደገፍ ሲል እጁ ባዶ ቦታ ላይ ያርፍና ለመውደቅ አንሰራርቶ ይነሳል...በሰከረ ዘዬ---አነጋገር መንፈስ...) አይ ይኼ የኛ ቤት! ዛሬ ደግሞ የቤታችንን ምሰሶ ነቅለሽ ጠበቅሺኝ....አንቺን እኮ ነው!!! ሁሌ ኩሽና፣ ማድቤት መጨናበስ....! አንቺ! እሺ ምሶሶውስ ይሁን አይኑር፣ ቆይ ግን ቤቱ እንዴት አለምሰሶ ቀጥ ብሎ ሳይወድቅ ቆመ!? ነው ወይስ ቤቱም የለም? (ቀና ብሎ አንገቱን እያዟዟረ ያያል...)
ሚስቲቱ(ትገባለች ከውጭ)፦ አይ እድሌ! አይ የ40 ቀኔ ዛሬም ገልብጠኸው መጣህ!? ምንም አትመጣም...ከምንም ተቆጠርኩ ማለት ነው?
ሰካራሙ(ባል)፦ እስቲ ዝም በይ! ንግግር አሳመርኩ ብለሽ አትዘባርቂ....ሲጀመር አንቺ የ80 ቀን እድል እንጂ የ40 የለሽም! የ80 ያዬ በይ ካልሽም አሁን እኔ ምለው ቤቱ እንዴት አለምሰሶ ቆመ? "ቤት አለምሰሶ ሀገር አለካስማ " ሲባልም ነው የማውቅ ፤ ይኸው አንቺ ግን ጎጆይቱን አለምሶሶ አቁመሽ ድንቅ፣ እጹብ ድንቅ ከላሊበላም የሚልቅ ቅርስ አቆምሽ። አረግ የዘንድሮው መጠጥ ደግሞ
ፈላስማ ሲደመር ፖለቲከኛ እኩል ይሆናል እብድ ነው የሚያረግ መሠል ነገሬን አረቀኩብሽ.......

(ተዉኔቱን ስትደርሱ በየትኛውም የሃገራችን ዘዬ ማድረግ ትችላላችሁ።)

እንደ መነሻ ይህን አልኩ እናንተ ደግሞ በመቋጨት፣ ከኔም በላይ በተሻለ መነሻ ሃሳብ በመድረስ ክሂሎታቹን አዳብሩት እላለሁ።

ለማናገር ከፈለጋቹ

@godbl____who

ቀ ላ ል➘➘➘
@gbw_dan


♡ ㅤ   ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ

ይቀላቀሉን

https://t.me/gbw_dan
1.4K viewsዳኒ, 14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 12:17:31 ተነጣጥሎ ያለው የቅዱሳን ጸጋ
ማርያም ጋ ረጋ።

ኤልያስ ሽታኹን

~ ~ ~ ~ ~
ነብያት ይላሉ
"ፈኑ እዴከ እም አርያም"
እጁ ብቻ ያይደል
ስው ሆኖ ተገኘ እግዜር ከማርያም።

እግዚአብሔር ከሰው አንድ ሰው ፈለገ
ልቡ እንደእዮብ ነፍሱ እንደዳዊት የተመነደገ

እንደአብርሃም ቀና እንደኖኅ አሳቢ
እንደሙሴ ያለ ያገር ልጅ ሰብሳቢ
በተግባሩ በስም
ንጉሥም ቅዱስም
ሁሉንም የሆነ።

እግዚአብሄር አየ
ለመንግሥቱ ለየ
ከሔዋን ዘር ሔዋን
ያልበላች ፍርዋን
እግዚአብሔር ለየ
በማርያም ታየ።

ተነጣጥሎ ያለው የቅዱሳን ጸጋ
ማርያም ጋር ረጋ።

እግዜር ሰው ከእንዲሆን
ዓለሙን እንዲምር
ማርያም
ተገኘች የቅዱሳን ድምር።
የምድር ኪሩቤል
የምድር ሱራፌል
ወልደአምላክ መንበር
በሁሉ የሞላ ተዘጋጀለት በር::

ወላዲተአምላክ
ጌታዬን አሰብኩት ለእናቱ ሲላክ።

ኦ ማርያም ትንቢተ ነብያት
ኦ ማርም ጾመ ሐዋርያት
ከዚህ ሁሉ ዓለም ልቡ ከታበየ
አንድ እርሷ ተገኘች ማርያም ርግብየ::
ርግብየ
ርግብየ
ርግብየ ልቧ በትህትና ክንፍ
ገርድ ልሁን ስትል አምላኳን ስታቅፍ

ይህን አንድ ሚስጢር ተጽፎ ቢያየውም
ተደርጎ ቢያየውም
ራሱን ይህ ምስጢር ዓለም አይችለውም።

እሙ ለፀሀዩ ትህትና ነፍሷ
ማነው የሸመነው የማርያም ቀሚሷ?

እንደምስኪን ጎንበስ
የሰው ዕንባ ማብስ
"ንግሥት ናት" ብሎ ሰው ልኳን ቢገምት
የጌታዬ እናት ግን እንደድሀ ኩርምት።

ተበታትኖ ያለው የቅዱሳን ጸጋ
ማርያም ጋር ረጋ።

እግዜር ሰው ከእንዲሆን
ዓለሙን እንዲምር
ማርያም ተገኘች የቅዱሳን ድምር።

@frombooks1234
꧁༻༒༺꧂ ‌‌
1.5K viewsዳኒ, 09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 22:04:44 ባትመጣም ቅጠረኝ
ከለመድኩት ቦታ በለመድኩት ሰአት
ናፍቀኸዋል እና አይኔም ሲንከራተት
...አንተኑ ለማየት
ዛሬም እንደወትሮ መሆኑ ሳይጠፋኝ

...... ሁሉን እያወኩት
ሰአቴን ቆጥሬ ራሴን ኳኩዬ
ከቀጠርከኝ ቦታ ደረስኩ ተቻኩዬ
እንዳላረፍድብክ ተገኘሁ ቀድሜ
እስክትመጣ ብዬ ሰአቱን ለመግደል
ማሰቤን ጀመርኩኝ ስትመጣ እምልህን
.
እንዴት እንደማይህ
ምን እንደማወራህ
አቀማመጤንም ላንተ ሳይደብርህ
ደርሶ እንድማርክህ።
አስተካከል ጀመር
ከመጣህ ቡሃላ በራሴ እንዳላፍር
.
ደቂቃዉ ቀን ሆነ እጅጉን በዛብኝ
ደጋግሜም ባየዉ አልገፋ አለኝ
ብቻ ምን ልበልህ ብቻዬን ቁጭ ብዬ
ፀሃይ ዝናብ ብትል ሙቀትና ብርዱ
.. ....ዋለብኝ ከላዬ
ግና ምን ዋጋ አለዉ፦
ለኔ ያንተ መምጣት
ህልም ብቻ ከንቱ ምኞት
አንድ ሆኗል ጉም ከመጨበጥ።
..
ዛሬም ሞኟ ብናፍቅህ
ያንተ መሆን ብጓጓልህ
ረሳሁት ያን ህመሜን
ስጠብቅህ በመቅረትህ ያየሁትን
ደግሜ አልኩህ ባትመጣም
አዲስ ባይሆን ሁሉን ባውቅም
አይን አይንህን እያየሁኝ
ካፍህ ይውጣ ተናገረኝ
በቃ ሁሌ ..ይልመድብኝ
.
ባትመጣም ኔን ቅጠረኝ
ስሞትልህ ተስፋ ስጠኝ

ተፃፈ መኒኒኒኒ
የደሱ ግጥሞችና

@frombooks1234
꧁༻༒༺꧂ ‌‌
1.3K viewsዳኒ, 19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 15:52:55
@frombooks1234
꧁༻༒༺꧂ ‌‌

በገበያ ላይ....በጃፋርና በተለያዩ የመጽሐፍት መደብር በገፍ፣ ነፍፍፍ

ሆኖ ያገኙታል!ይወዱታል!
1.4K viewsዳኒ, edited  12:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 17:56:59 °°\\ኤልያስ ሽታኹን °°\\
ማሰብና ማመን ወደአፍሪቃ መጡ
በውጊያ ምክንያት
መቆም አቃተቸው እንኳ ሊቀመጡ፡፡
ሁሉ ውጊያ ላይ ነው
በየስም አጠራር
በጦር አመራር፡፡
የጥቁር ዘር ታሪክ በሞት የዘመነው
ክላሽ እንደቆሎ ማነው ያዘገነው?
ብለው ሊጠይቁ
በውጊያ መካከል ሞትን ሲጋፈጡ
የሚተኩስ እንጂ
ቆም ብሎ ሚያወራ አንድ ጥቁር አጡ፡፡
* አንዱን እንደምንም
ጠየቁት አቁመው
ስሙን ረስቶታል ስሙ የቡድን ነው፡፡
ገና ነው
ህፃን ነው
እንኳንና መግደል
ቁራሽ አለመስጠት የሚመስለው በደል ::
ነበር፡፡
* ህፃን ነው ተማሪ
የአስኳላ ጀማሪ
ጠላትና ወዳጅ እንደተምታታበት
ጥያቄው ሳይገባው ጠላት ደረሰበት፡፡
* አንዷን እጇን ያዟት
ለመኗት
ዘከሯት
እሺ ብላ ቆመች
ምላሹ ሲከብዳት አዙራው ደገነች፡፡
አንበረከካ
አስራ
ትታቸው ሮጠች
ጦርነት ስራ ነው አፍሪቃም አይደለች፡፡
ሐበሻ ብልሁ
ሐበሻ በእልሁ
እየለዋወጠ የሞቱን አሟሟት
ቁጭ ብሎ ያያል
በነጴጥሮስ ሀገር ጭካኔን ሲሾሟት፡፡
ሐበሻ ብልሁ
ሐበሻ በእልሁ
የሆዱን ለጀርባው አዙሮ እያዘለ
በቀን የሰራውን
ማታ ይሰማዋል ዜና ነው እያለ ፡፡
ሐበሻ ብልሁ
ሐበሻ በእልሁ
እምነቱን ለገዳም
ሀጢያቱን ለአዳም
ወስዶ እየለደፈ
ፆሙን ይቀበላል ሰው እየገደፈ፡፡
ማመንና ማሰብ
ወደአፍሪቃ መጡ
መቆም አቃታቸው እንኳን ሊቀመጡ፡፡
ሰውና ጠምነጃ ፀንቶ ትዳራቸው
ሞትን እንዲወልዱ ማነው ያስተኛቸው፡፡
ባሩድ ባለጉልበት እየተጀመረ
እየተካረረ
በፀብ በክርክር
ለመኖር ይላል የሟቾች መፈክር፡፡
በመላው አፍሪቃ ተፅፎ ምታየው
ትልቁ መፈክር እንደዚህ የሚል ነው፡፡
ማሰብ እንኳን ካሰብክ ማሰላሰል በውል
እንያንዳንህ ዜጋ
ከመነጽርህ ጋር ጠመነጃህን ወልውል፡፡
እረ የኛስ ሊቅ
እረ የኛስ ምሁር
ካልደፈራረሰ አይጠራም እያሉ እያደፈረሱ
እድሜ ለመፈክር
የወለዱ ሁሉ በባሩድ ታረሱ፡፡
ሞት በጥቁሮች መሬት የተበራከተው
እድሜ ለመፈክር
ቆም ብሎ ማሰብ ስለሚያስገድል ነው፡፡
እንዲያ ነው መናናቅ
እንዲያ ነው መራራቅ
በነፍስም በስጋም በመንፈስ ሳይኖሩ
እንደምን ቻልንበት ጦርን መወርወሩ፡፡
የለንም ከስጋ
የለንም ከመንፈስ
እንዲያው ብቻ




በነፍስ ጠፍተናል
የፈጠረን አምላክ በስም እስኪረሳን
እድሜ ለመፈክር
ለፍቅር ተኝተን ለቀብር ተነሳን ፡፡
ቆም ብሎ ማደግ
ሰከን ብሎ መኖር
አበቦች በለጡን
እንስሶች በለጡን
እሾህዎች በለጡን
ሞት ሆነን በቀልን ባሩድ እያጠጡን፡፡
ወከባ እያጠጡን
ጥድፊያን እያጠጡን...
የሞት ወርቅ በላን
የሞት ብር በላን
የሞት ነሀስ በላን
ከእናታችን ጉያ ጫካ ነው የደላን፡፡
እወራረዳሁ
በክላሽ ያፅናኑት
በመውዜር ያዳኑት
ጠባሳው እንዲሽር ሬት ቀብተውት
አበስነው ይሉሀል ጭራሽ አብሰውት::
እወራረዳለሁ
ግድ የለም እንስከን
ግድ የለም አንስከር
ህይወት ምን ቢያቅረን
ሞት እንኳን ይምከረን፡፡
እወራረዳለሁ
የሚወደቀው ሰው ነው
የሚሞተው ሰው ነው
የሚረግፈው ሰው ነው
እንደጫካ ቅጠል
የኛ እኮ አኗኗር
ከችግር ለመውጣት ከችግር መቀጠል፡፡
እወራረዳለሁ
ያለበደላቸው
ያለነውራቸው
ተስፋቸው ተቀብሮ ህልማቸው በሞተው
የአፍሪቃ ወንበር
እንባ ላይ ሆኖ ነው መፅናት የሚያቅተው፡፡
እንዲያ ነው ሲርቁት
እንዲያ ነው ሲንቁት
ሁሉን ገዢ አላህ ሁሉን ገዢ እግዜር
ሰላም ላምጣ ይላል ጠመኔጃና መውዜር፡፡
እንዲ ነው ሲንቁት
እንዲያ ነው ሲርቁት የዓለማትን ጌታ
ላስታርቃችሁይላልሰይጣን በቄስ ቦታ።


@frombooks1234
꧁༻༒༺꧂ ‌‌
1.4K viewsዳኒ, edited  14:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 15:30:38 ​ ሥርዓተ ንባባት ዘልሳነ ግእዝ
| ማጠቃለያ - ፪ | 2


____ ፫. ተጣይ
• ዝንቱ፡ሥርዓተ፡ንባብ፡ይትነገር፡ኲለሄ፡በሳድስ፡ፊደል።
- መጨረሻውን በሳድስ ፊደል ብቻ ያረጋል።

• መነሻ ፊደላቸውን በግእዝ ፣ በካዕብ ፣ በሣልስ ፣ በራብዕ ፣ በኃምስና በሳድስ ያረጋሉ ፡፡

ምሳሌ ፦
አዶኒስ
ናብሊስ
ዑራኤል
ሩፋኤል
ጊዮርጊስ
ሚካኤል
ሲኖዶስ
ኤልሳቤጥ
ኤልዛቤል
እግዚአብሔር
እስጢፋኖስ
እስክንድር ........ወዘተርፈ


____ ፬. ሰያፍ
• ይኽም የንባብ አይነት በሳድስ ብቻ ይጨርሳል።
• ሲነበብ እንደ ተነሽ ንባብ ተመሳሳይ ሲሆን ድምፅን ከፍ በማድረግ ነው።
• በስምና በአንቀጽ ይገኛል።

ለምሳሌ ፦

▹ በስም
አብርሃም
ያዕቆብ
ገብርኤል
ማቴዎስ
ዘካሪያስ
ዮሐንስ

▹ በአንቀጽ
ቀዳማይ ፣ ካልዓይ ፣ሣልሳይ

ገብረ ይገብር ይግበር
ቆመ ይቀውም ይቁም
ሰከበ ይሰክብ ይስክብ


ለዮም፡የአክለነ። ሠናይ፡ጊዜ።
(ለዛሬ ይበቃናል መልካም ጊዜ)
#ሥርዓተ_ንባብ #ማጠቃለያ

ቀ ላ ል➘➘➘
@gbw_dan

♡ ㅤ  ❍ㅤ     
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ Turn on
1.0K viewsዳኒ, 12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 05:59:32 (credited አብርሃም ፀ.)

ንባብ
-----
ከመጽሐፍ በብዙ የራቁ ሰዎችን አትመን ፤አውቀው ባይጎዱህ እንኳን ባለማወቅ ይገድሉሃል ወይም ያስገድሉሃል።

– Lemony Snicket

የአንድ ማኅበረሰብን ባህል ለማውደም ከተፈለገ መጻህፍትን ከማቃጠል ይልቅ የማያነቡ ትውልዶችን መፍጠር የበለጠ ወጤታማ መላ ነው።

– Ray Bradbury

ሰዎች ኢሞራላዊ ብለው የሚፈርጇቸው መጻሕፍት ካሉ የነዚህ መጻሕፍት ደራሲዎች የዓለምን ነውር እያጋለጡ እንደሆነ ጠርጥሩ።

- Oscar Wilde, The Picture of Dorian Gray


በአሁን ጊዜ ጸሎት ሊደረግላቸው ከሚገቡ ነገሮች መካከል አንዱና ዋንኛው የቴሌቪዥን መቀመጫ ቦታን በመጽሐፍ መደርደሪያ ስለመተካት ነው።

– Roald Dahl

ከመናገር በፊት ማሰብ ይገባል ቢባልም ከማሰብ በፊት ግን ንባብ ሊኖር ግድ ነው። ዓለማችን በበርካታ ረብ የለሽ ንግግሮች እየተወረረች ያለችውም በዚህ ምክንያት ነው።

- Fran Lebowitz

ሰዎች ሁሉ ተስማምተው በሳምንቱ ቀናት ላይ ለንባብ ብቻ የሚውል ስምንተኛ ቀን ሊጨምሩ ይገባል።

- Lena Dunham

ጥሩ መጻህፍትን ማንበብ ከቀደሙ ዘመናት ልሂቃን ጋር ቁጭ ብሎ እንደመጨዋወት ነው።

- Descartes

የማያነቡ ሰዎች ከዓለም የትናንትና ታሪኳ፣ ከነገ ሕልሟና ከዛሬዋ ማንነት የተገለሉ ባይተዋር ናቸው።

- John Green

ግራ ገብቶህ መወሰን ባቃተህ ጊዜ መላ ይዞ የሚደርስልህ ትናንት ስታነበው የኖርከው መጽሐፍ ነው።

- Oscar Wilde

መጻሕፍትን አንብበው ወደየትም ሥርቻ ወርውረዋቸው ሊሆን ይችላል፤ አኩርፈው ግን ጀርባ የሚሰጡ ወዳጅ አይደሉም። ዋጋ ከሰጧቸው ደግሞ የዘላለም አፍቃሪዎ ናቸው።

- John Green

@frombooks1234
꧁༻༒༺꧂ ‌‌
1.4K viewsዳኒ, 02:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 14:57:43 @@@_ኢፒክ_Epic_@@

ስለአንድ አገር ብሔራዊ ጀግና ወይም በአፈታሪክና በሃይማኖት ተጋዳይና ታዋቂ ስለሆነ ወይም ገድል ማለት ነው። የጀግንነት ግጥም ብዙ መነሻ ምንጮች ሲኖሩት፣ ዋና ዋናዎቹ ተረት፣ እምነት፣ እንቆቅልሽ፣ ሽለላና ቀረርቶ፣ ሃይማኖት፣ አፈታሪክ፣ ስነ-ቃልና ታሪካዊ ድርጊቶች (ክስተቶች) ናቸው። በዚህ አይነት የጀግንነት ሥነግጥም ከአንድ አገር ህዝብ የተጋድሎና የጀግንነት ህይወት ጋር የሚያያዝ ሲሆን ረጅም የታሪክ ሂደትን ማለት ድልን ወይንም ሽንፈትን ይዳስሳል። ይህ የግጥም አይነት ስለ ጀግና ሰዎች ድርጊት፣ ስለ ታሪካዊ ቦታዎችና ክስተቶች ብዙ እንድናውቅ የሚያስችለን የሥነጽሑፍ አካል ነው።
ኢፒክ በሁለት ዓይነት መንገድ የሚታይ ሲሆን በአፍአዊ እና በፅሁፋዊ ትንታኔም የሚቀርብ ነው። በአፍአዊ ሥነጽሑፍ የጀግንነት ግጥሙ ደራሲ አይታወቅም። ሥነጽሑፋዊ ኢፒክ በስድ ጽሁፍ (በዝርው) እና በግጥም መልክ በብዛት ተፅፎ ይገኛል።
ከጀግንነት ግጥሞች ሁሉ ቀዳሚ ወይም ጥንታዊው በአሶርባኒፖል ቤተመጻሕፍት ውስጥ የተገኘው የጊልጋሜሽ የጀግንነት ግጥም(The Epic of Gilgamesh) ነው።

ኢፒክ(ዘመን አይሽሬ የስነጽሁፍ ቅርስ) በታደለ ገድሌ
ገፅ ከ1-2?

@frombooks1234
꧁༻༒༺꧂ ‌‌
1.4K viewsዳኒ, 11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ