Get Mystery Box with random crypto!

የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የ8ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ በኢንተርኔት ላይ ማየት እንደሚቻል | Free Education Ethiopia ✔️︎

የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የ8ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ በኢንተርኔት ላይ ማየት እንደሚቻል አስታወቀ።

ቢሮው የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መውጣቱን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ በክልሉ 451 ሺሕ 21 ተማሪዎች ለፈተና የተመዘገቡ ሲሆን 98 ነጥብ 3 በመቶ የሚሆኑት ፈተና መውሰዳቸውን ገልጿል።

በዚህም የ9ኛ ክፍል የማለፊያ ውጤት ለወንዶች 50 በመቶ እና ለሴቶች 47 በመቶ ነው ብሏል።

በአርብቶ አደሩ አካባቢ የ9ኛ ክፍል ማለፊያ ውጤት በመቶኛ ለወንዶች 47% ለሴቶች 44% ሲሆን ለልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ደግሞ ለወንዶች 44% እና ለሴቶች 41% መሆኑም ተገልጿል።

ማለፊያው ውጤት በአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ እና በትምህርት ጥራት ላይ ተመስርቶ መወሰኑን የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ግርማ ባይሳ ገልጸዋል::

ሴት ተማሪዎች የተሻለ የፈተና ውጤት በማምጣት ለውጥ አምጥተዋልም ነው ያሉት።

ተማሪዎች ውጤታቸውን በኢንተርኔት ላይ ‘https://oromia.ministry.et/#/home ላይ መመልከት ይችላሉም ነው የተባለው።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!