Get Mystery Box with random crypto!

በድጋሚ ሙስሊም ወሎዬዎች ተጨፈጨፉ =========================== Majlisa Oro | ፈትህ አባቦራ መስጂድ

በድጋሚ ሙስሊም ወሎዬዎች ተጨፈጨፉ
===========================

Majlisa Oromiyaa - የኦሮሚያ መጅሊስ - Oromia Mejlis

በቄለም ወለጋ ዞን በመቻራ ወረዳ መንደር 20 ቀበሌ ውስጥ በወሎ ሙስሊሞች ላይ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ተፈፅሟል። ኢናሊላሂ ወእና ኢሌይሂ ራጂኡን። ቁስለኞች ሆስፒታል አጨናንቀዋል። የሟቾች ቁጥር ብዙ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመልክታል። ከማህበረሰቡ የደረሰን መረጃ በኦነግ የታጣቂዎች እንደተፈፀመ አሳውቀውናል። ታጣቂዎቹ በቅርብ ግዜ በምዕራብ ወለጋ ቶሌ ወረዳ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ተጨፍጭፈዋል። ተፈናቅለው ያሉትም አስፈላጊ እርዳታ አልደረሳቸውም። የወሎዬዎች ሞት መች ያበቃ ይሆን ሃላፊነቱስ ማን ይወስዳል
ለፖለቲካ ፍጆታ ለምን የሙስሊሞች ደም ይፈሳል እስከመቼ
የኦሮሚያ መጅሊስ ድርጊቱን አጥብቆ ያወግዛል። ሀገርን እያስተዳደረ ያለው መንግስት ነው። ስለዚህ ይህንን ጉዳይ በአስቸኳይ አጣርቶ የማያዳግም እርምጃ እንዲወስድ አጥብቀን እንጠይቃለን። የቶሌ ጉዳይ ፈር ሳያገኝ በድጋሚ መከሰቱ አሳፋሪ ነው።
የአላህ ወንድሞቻችን የሸሂድነት ደራጃ የቆሰለቱን ፈውስን ለቤተሰባቸው ሰብርን ወፍቃቸው። አሚን


https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia