Get Mystery Box with random crypto!

FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

የቴሌግራም ቻናል አርማ fdredefenseforc — FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት F
የቴሌግራም ቻናል አርማ fdredefenseforc — FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
የሰርጥ አድራሻ: @fdredefenseforc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.52K
የሰርጥ መግለጫ

# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-13 14:35:31 ከኮሩ ክፍሎች ለመጡ የጤና ሙያተኞች የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ረዳትነት ትምህርት እየተሰጠ ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 05 ቀን 2016 ዓ.ም     
    
የኮሩ የጤና ክፍል ሃላፊ ሌተናል ኮሎኔል መኮነን ሞላ  መደበኛ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ረዳት ሰልጣኞች የሰራዊቱን ጤንነት ለመጠበቅ ለተልዕኮ አፈፃፀም እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ተላላፊና ተላላፊ የልሆኑ ወረርሽኝ በሽታዎች እንዳይከሰቱ ቀድሞ ለመከላከል ታስቦ እየተሰጠ ያለ መሆኑን ገልፀዋል።

በሀገሪቱ የጤና ፖሊሲ መሠረት የመከላከያ ጤና ዋና መመሪያ የጤና ተማሪዎች ማወቅ ያለባቸውን ሙያ እንዲጨብጡ በማድረግና ያወቁትን ዕውቀት በሰራ ላይ ማዳበር እንዲችሉ ታሳቢ ተደርጎ የሚሠጠው ሙያዊ ሥልጠና ተገቢ መሆኑንም አሥረድተዋል።

ለሠራዊቱ ቀልጣፋ የህክምና እርዳታ ለመስጠትና በተለይም ደግሞ የቅድመ በሽታ መከላከል ስራዎችን በተገቢው ለመስራት ሠልጣኝ የጤና ሙያተኞች ከነባር የጤና ባለሙያዎች ጋር በቅንጅት መሥራት እንደሚገባቸው ተናግረዋል።
 
ዘጋቢ ሱራፌል መልሰው
ፎቶ ግራፍ ሱራፌል መልሰው

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
5.6K views11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-13 14:35:26
5.2K views11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-13 12:43:34 ህብረብሔራዊነታችንን በማጠናከር ለሁሉም የምትመች ሀገር እንገነባለን በሚል መሪ ቃል የሰላም ኮንፈረንስ በሊበን ጭቋላ ወረዳ ተካሄደ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ግንቦት 05 ቀን 2016 ዓ.ም

በምስራቅ ሸዋ ዞን በሊበን ጭቋላ ወረዳ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በጥምር የፀጥታ ሃይሉ የሰፈነውን ሰላም  እናፅና ለሰላማችን ዘብ መሆን ያለብን እኛው ነን፤ ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት ነው ፤መከላከያ ሠራዊቱ  መስዋዕትነት እየከፈለ የሚያረጋግጠውን ሰላም ማስቀጠል የእያንዳንዱ ማህበረሰብ ሃላፊነት ነው ሲሉ የምስራቅ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አት አባቡ ዋቆ ገልፀዋል ።

ይህንን ሰላም ለማረጋገጥ ፅሀይና ዝናብ እየተፈራረቀባቸው የህዝብን ሰላም ለማረጋገጥ ህይወታቸውን እየገበሩ ላሉ ለመከላከያና ለመላው የፀጥታ ሃይሎቻችን ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

በኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የክፍለጦር ዋና አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ሳሊወን ክብረሃሰን በበኩላቸው አካባቢውን ሰላም ለማድረግ በቁርጠኝነት እየሰራን ቆይተናል ፤ አሁንም ወደፊትም መስዋዕትነት እየከፈልን የህዝባችንን ሰላም ለማረጋገጥ ላፍታም ቢሆን አንዘናጋም ፤ አሸባሪው ሸኔም እጁን ካልሰጠ በገባበት እየገባን እናጠፋዋለን ሲሉ ተናግረዋል።

የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ደበሌ ነጉ የወረዳው ነዋሪዎች የሰላሙ ባለቤት እኔው ነኝ ከሰላሙ የምጠቀመው እኔው ነኝ በማለት ለዚህ ኮንፍረንስ መሳካት ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግነው ለተግባሩም ሁሉም በቅንነት መስራት እንዳለበት ገልፀዋል።

ዘጋቢ አባተ ወልደእየሱስ
ፎቶ ግራፍ ጥላሁን አለሙ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም 
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
5.8K views09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-13 12:43:31
5.5K views09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ