Get Mystery Box with random crypto!

ክረምቱ መጥቶ ወደ ሰማይ ሽቅብ አንጋጥቼ ስመለከት የጠቆረው ዳመና ልቤን ያስታውሰኛል ጭጋጉንም ሳይ | GRACE FAMILY

ክረምቱ መጥቶ ወደ ሰማይ ሽቅብ አንጋጥቼ ስመለከት የጠቆረው ዳመና ልቤን ያስታውሰኛል ጭጋጉንም ሳይ ኅጢአት ያጠለሸው ልቤ ፊቴ ላይ ድቅን ይላል ከዛ ደግሞ እርጥበቱ ሞልቶ የዝናብ ነጠብጣቦች ሲወርዱ በንስሀ ልብ ያፈሰስኳቸውው እንባዎቼ ትዝ ይሉኛል

ለጥቆም ዝናቡ ሲያበቃ የጠቆረው ዳመና ቀለል ብሎ ሳየው ከንስሀ በኃላ የሚሰማኝን እረፍት ያስታውሰኛል ከሰዓታት በኋላ ግን መልሶ ሰማዩም ይጠቁራል የእኔ ልብም እንዲሁ።

በዚህ የማያልቅ ዑደት ውስጥ ኅጢአቴ ደጋግሞ በብርድ አንዘፈዘፈኝ ግን የሚያሞቀኝ አንድ ፅኑ ተስፋ አለኝ በዚህ ውጥንቅጥቅ ውስጥ እንኳን አቅንቶ የሚያቆመኝ። "እሄዳለው ወደዛች ሀገር ወደ በጉ ከተማ" የሚል ፅኑ ተስፋ

ብርድም ሙቀትም ወደ ሌለበት ክርስቶስ ብቻ ወደሚያበራበት ሀገር በእሱ ወደሚደምቀበት ደመና እና ጭጋግ ክረምት እና በጋ ቀን እና ማታ ፍፁም ወደ ሌለበት ወደ በጉ ከተማ ልሄድ እጅግ ናፍቄአለው በቃ የኅጢአት ደመና ልቤ ላይ አይደምንም እንዴት ደስ ይላል!

Macarthur አንዴ እንዲህ ብሎ ነበር "መንግስተ ሰማይን ሳስብ የሚያጓጓኝ በወርቅ የተለበጡት በእንቁ የተዋቡት መንገዶች ሳይሆኑ የኅጢአት አለመኖር ነው" የእኔም ጉጉት ይሄ ነው ኢየሱስ ቶሎ ና