Get Mystery Box with random crypto!

#ጥንቃቄ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በተገኘ መረጀ በሐምሌ የመጀመርያዎቹ ሳምንታት | ሰበር ዜና ETHIOPIA

#ጥንቃቄ

ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በተገኘ መረጀ በሐምሌ የመጀመርያዎቹ ሳምንታት ከፍተኛ የሆነ ነጎድጓዳማና በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ይኖራል።

በተከታታይ ቀናት የሚኖረው የዝናብ መጠን ጎርፍና የመሬት መንሸራተት ሊፈጥር ስለሚችል አስፈላጊው ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል፡፡

በአርብቶ አደር አካባቢዎች የሚገኘውን ውኃ በጥንቃቄ መያዝም እንደሚገባ ተገልጿል።

የሚፈጠረው ዝናብ ከመጠን በላይ ማሣ ላይ ውኃ እንዲተኛ ስለሚያደርግ በእርሻ እንቅስቃሴው ላይ አሉታዊ እንቅስቃሴ እንዳያስከትል የማጠንፈፊያ ቦዮችና የጎርፍ መከላከያ እርከኖች በመሥራት ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ከመደበኛ በላይና መደበኛ ዝናብ የሚጠበቅባቸው ቦታዎች ፦
- አፋር፣
- አማራ፣
- ትግራይ፣
- ኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች መሆናቸውን ኢንስቲትዩቱ አሳውቋል።

በተለይም ለጎርፍ ተጋላጭ የሆኑ ማለትም ተዳፋትና ገደላማ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የክረምቱ የዝናብ ሁኔታ በሐምሌና ነሐሴ ወራት እንደሚጠናከር የሚጠበቅ ሲሆን መብረቅ፣ ጎርፍና የበረዶ ግግር ሊኖር ስለሚችል ማኅበረሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል ተብሏል።

መረጃውን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩትን ዋቢ አድርጎ ሪፖርተር ነው ያጋራው።