Get Mystery Box with random crypto!

የ ኢትዮጵያ ቡና የማሊያ ርክክብ ! ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀ እስከ ፐ ከተሰኘ የትጥቅ አምራች ኩባንያ | Ethiopia buna sport clubʳ

የ ኢትዮጵያ ቡና የማሊያ ርክክብ !

ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀ እስከ ፐ ከተሰኘ የትጥቅ አምራች ኩባንያ ጋር ዛሬ የትጥቅ ርክክብ ስነ-ስርዓቱን በ ሳፋሪ ሆቴል አከናውኗል ።

ከ ሀ እስከ ፐ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ላለፉት አምስት አመታት በጋራ የሰራ ሲሆን ኢትዮጵያ ቡና አዲሱን ማሊያ በሁለተኛው ዙር የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ እንደሚጠቀምበት ተገልጿል ።

ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀ እስከ ፐ ጋር በጋራ በመሆን አራት ኪሎ አምባሳደር ህንፃ ላይ አዲስ የትጥቅ መሸጫ ሱቅ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚከፍት ገልጿል ።

በትጥቅ መሸጫ ሱቁ ላይ ከክለቡ ማሊያዎች በተጨማሪ የክለቡ አርማን የያዘ የተለያዩ ኮቶች እና ልዩ ልዩ አልባሳት እንደሚሸጡ ተገልጿል ።

ከ ሀ እስከ ፐ ለ ኢትዮጵያ ቡና ዋናው ቡድን ፣ ከ 20 አመት በታች ፣ ከ 17 አመት በታች እና ለ ሴቶች ቡድን በአጠቃላይ 500 ማሊያ እንደሚያቀርብ ተገልጿል ።

ከ ሀ እስከ ፐ ለ አሰልጣኞች ከ መቶ በላይ እና ለአሰልጣኝ አባላት 50 የክለቡ አርማን የያዙ ማሊያዎችን እንደሚያቀርብ ተገልጿል ።

በ አጠቃላይ ከ ሀ እስከ ፐ ለ ኢትዮጵያ ቡና ያቀረባቸው ትጥቆች ዋጋ ሶሰት ሚሊየን 25 ሺህ ብር እንደሆነ ተገልጿል ።

ከ ሀ እስከ ፐ ከዚህ ቀደም የሀበሻ ቢራን የብራንድ የትጥቅ መሸጫ ሱቅን የከፈተ እና በዘርፉ ላይ የስምንት አመት ልምድ ያለው ሲሆን በ ኢትዮጵያ ቡና ማሊያ እጅጌ ላይ የድርጅቱ አርማ እንደሚቀመጥ ገልጿል ።

@ethiopiabuna12t
@ethiopiabunasportteam