2022-07-15 22:48:22
መልካሙ ዶክተር
ክፍል ሁለት
አቅራቢ ብሩክ
ሃኪም ቤት የካርድ ብር አጥቼ ወዲህ ወዲያ ስል አንዲት
መልካም እናት ልጄ ሰው ጠፍቶብሽ ነው ወይ ብለው ጠየቁኝ እኔም የሆነውን ነገር ሁሉ በትህትና ነገርኳቸው፣ እርሳቸውም አይዞሽ ልጄ አንቺ መልካም ልጅ ነሽ የካርዱን ብር እኔ እሰጣችኋለሁ ግን የህክምና ብር አለሽ ወይ ብለው ጠየቁኝ
ማዘር እኔጋ ምንም ብር የለም ምናልባትም ልጁ ቀድሞ
እራሱን ቢያውቅ ስልክ ቁጥር ተቀብለን ለቤተሰቦቹ መደወል
እንችል ነበረ አልኳቸው
መልካም ብለው እርሳቸውም ከእኔ ጋር አብረው የልጁን ሁኔታ
ለማየት ቁጭ አሉ
ዶክተሩ የመጀመሪያ እርዳታ ከሰጠ በኋላ ለጊዜው ብዙ
አሳሳቢ ችግር እንደሌለበት ነገር ግን እራሱን ከጭንቀት ነጻ
ማድረግ እንዳለበት ነግሮት አንድአንድ መድሃኒቶችን ሰጥቶ
ትንሽ ብር ሲጠይቅ እኔ ቶሎ ብዬ ቤተሰብ ጋር ልደውል ስልክ
ቁጥር ስጠኝ አልኩት
ከዝምታ ሌላ ምንም መልስ መስጠት አልቻለም
በዚህን ጊዜ ከልጁ ዝምታ የሆነ ነገር መረዳት የቻሉት እናት
ከቦርሳ ውስጥ አውጥተው ሃኪሙ የጠየቀውን ብር ሰጡ
በጣም ደስ አለኝ ግን ምን አይነት መልካም እናት ናቸው?
ከዛም ልጄ እኔ አሁን ወደ ቤት ልሄድ ነው እናንተም ወደ
ቤታችሁ ተመለሱ ይሄ የታክሲ ብር ነው ብለው ብዙ ብር ሊሰጡ
ሲሉ እማማ እኔ ምን ቤት አለኝ ብለው ነው ለኔ የሄድኩበት ሁሉ
ቤቴ ነው የትም ሰፈር ብሄድ መኖር እችላለሁ ብሩን ለሱ
ስጡት አልኳቸው ልጄ ምን እያልሽ ነው ቤት የለኝም ማለት ምን ማለት ነው?
ቤተሰብ አለሽ አይደል ብሎ ጠየቁኝ እማማ ለካ እርስዎም ቀልደኛ ኖት ቤተሰብ ቢኖረኝ ይሄን
እመስላለሁ ብዬ ጥዬ ልሄድ ሲል ታዲያ ወዴት ነሽ ብለው ጠየቁኝ
ወዴት ነኝ? እኔን ከየት ነሽ ብሎ እንጂ ወዴት ነሽ ብሎ ሰው
ጠይቆ አያውቅም ምክንያቱም እኔ እግሬ ወደ መራኝ መሄድ
እንጂ እዛ እሄዳለሁ ብዬ መንገድ አልጀምርም አልኳቸው
ታዲያ ለምን ዛሬ ከእኔ ጋር አትሄጅም አሉኝ ቡሌ ይስጡኝ እንጂ የትም እሄዳለሁ አልኳቸው
ቡሌ ደግሞ ምንድነው ሲሉኝ
እማማ ምሳ አልበላሁም አልኳቸው
ልጁን አንተስ አትሄድም አሉት
እማማ እርሶ በጣም መልካም እናት ኖት ስለ ሁሉም ነገር
በጣም አመሰግናለሁ እግዚአብሔር ያክብሮት እኔ አሁን ቤት መሄድ እፈልጋለሁ እናቴ ትጠብቀኛለች ብሎ ልሄድ ሲል
ታዲያ ምስጋናው እኮ ከእኔ በላይ አጠገብህ ለቆመች ልጅቷ
ነው መሆን ያለበት እሷ እኮ ናት ከመንገድ ላይ አንስታ ሃኪም
ቤት የወሰደችህ አሉት
እሱም ወደ እኔ መጥቶ በመጀመሪያ ይቅርታ አድርግልኝ
ሃኪም ቤት የወሰድሽኝ አንቺ እንደሆንሽ አላወኩም ነበረ
በመቀጠል ደግሞ በጣም አመሰግናለሁ ስሜ እዩኤል ነው
ብሎ እጄን ጨበጠ
እኔም ሀረግ አልኩትና ለትንሽ ሴኬንዶች ሁለታችንም ፍዝዝ
ብለን ቀረን
በዚህ መሃል በይ አሁን እንሂድ እሱም ወደቤት ይሂድ ብሎ
እኔን ወደቤታቸው ይዘውኝ ሄዱ
ቤታቸው ደረስን፣ ቤት ውስጥ ለጊዜው ሌላ ሰው አልነበረም
ልክ ቤት እንደገባን የእጅ ውሃ ሰጥተውኝ ተሰርቶ ከተቀመጠው ምግብ አምጥተው ሰጡኝ
እኔም ተገኘ ብዬ ልጀምር ስል ቆይ ልጄ ምግብ ከመብላትሽ በፊት የሰጠሽን አምላክ ማመስገን አለብሽ ብለው አመስግነው
ሰጡኝ ምግቡን ግማሽ ካደረኩ በኋላ የእሳቸው ነገር ትዝ አለኝ
እማማ እርስዎ አይበሉም አልኳቸው እሺ መጣሁ አሉና ሌላ ምግብ አምጥተው ጨምረው ከእኔጋ አብሮ መብላት ጀመሩ
ይህች ቀን በህይወቴ ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ ሰዎች ክብር
የሰጡኝ ቀን ነበራች
ምግቡን ጨርሼ እማማ አመሰግናለሁ ብዬ ልሄድ ስል......
ይቀጥላል!
ከ 20 Like በኋላ ይቀጥላል
LIKE SHARE COMMENT
ከ20Like በኋላ ይቀጥላል
80 views19:48