Get Mystery Box with random crypto!

ስብዕናችን #Humanity

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiohumanity — ስብዕናችን #Humanity
የሰርጥ አድራሻ: @ethiohumanity
ምድቦች: ሳይኮሎጂ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 30.44K
የሰርጥ መግለጫ

🔆እየጠየቁ መኖር መልስን፣
መልስን ፈልጎ ማግኘት ዕውቀትን፣
እውቀት ነፃነትን፣ ነፃነት ሙሉ ስብዕናን፣
ሙሉ ስብዕና ሠላምና እርካታን፣
እርካታ ደግሞ ደስተኛ ሆኖ መኖርን ያስገኛል፡፡
አብረን እንደግ !!
@EthioHumanity @Ethiohumanity
✍የተሰማቹን አጋሩን! ቤቱ ሁሌም ክፍት ነው፣ሃሳባቹን ፃፍፍ አርጉልን @EthioHumanitybot

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-02-26 22:40:16 የማንን ግጥም ማንበብ ይፈልጋሉ?
1.3K views19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-26 20:37:08
የምታቀው የውሃ ኩሬ ራቅ ብለህ ስትመለስ ደፍርሶ ቢጠብቅህ...ንጹህ ውሃን ለመጠጣት ያለህ አማራጭ ድፍርሱ እስከሚጠራ መጠበቅ ብቻ ይሆናል ። "አፈር የተቀላቀለበትን ውሃ እንዲጠራ ከፈለግክ፤ተወው አታማስለው" ይላል ፈላስፋው አለን ዋትስ። በመተው፤በመረጋጋት፤ በዝምታ፤ ለፍተን ያጣናቸውን ውድ የህይወት ስጦታዎች እናገኛለን።

ልክ እንደዚህ ሁሉ በህይወታችን የሚገጥሙንን ችግርና እንቅፋቶችን አንዳንዴ የምናጠራቸው መሃል ላይ እጃችንን ስለከተትን ብቻ ላይሆን ይችላል ። አንዳንዴ ዝምታችን እና ትእግስታችንም ብዙ ነገሮች በራሳቸው ጊዜና ሁኔታ እንዲስተካከሉልን እድል ይሰጡልናል ። እኛ ችግራችንን ለመፍታት የምናደርገው ጥረት ይበልጥ ችግር ውስጥ እንዳይዘፍቀን መጠንቀቅ ይኖርብናል ። አለዝያ የችግሩ አሳዳጊ እና አባባሽ እንጂ የችግሩ ፈቺ አንሆንም ።

ለተረጋጋ አይምሮ አለም ትገበራለች ብሏል ጥንታዊው ፈላስፋ። ምንም እንኳን ብዙ ነገሮች በጥረትና በሩጫ የሚገኙ ቢሆንም፤ አንዳንድ ወሳኝ ነገሮች ግን በእርጋትና በመተው እንዲሁም በዝምታ የሚገኙ ናቸው።

ውብ  ምሽት

@EthioHumanity
@EthioHumanity
     
@EthioHumanitybot
838 viewsedited  17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 17:56:56
ሰዎች በየቦታው ፍጹም ትክክል መስለው ሲታዩ  ሰውኛ አይመስለኝም ። ከራሱ እየተቧቀሰ አካባቢው በቀረፀለት የትክክለኛነት ሳጥን ውስጥ የሚንፈራገጥ ሰው ራሱን ያጣ አሳዛኝ ይመስለኛል። ለእያንዳንዱ ነገሩ የሚጠነቀቅ ሰው ራሱን እየሆነ እንዳልሆነ ነው የሚገባኝ። ራስን መሆን እርማት አይጠይቅም። ራስን መሆን ጥንቃቄ አያሻም። መጠኑ ቢለያይም ሁላችንም ጋ ጥቂት እብደት፣ ጥቂትም ስህተት፣ ጥቂትም ፀፀት እና ጥቂትም ውድቀት አለ ብዬ አስባለሁ።

እውነታው ሰዎች ሊያወድሱህ ከፈለጉ ከፈጣሪ ታናሽ ያደርጉሃል ። ሊዘልፉህ ከፈለጉ ደግሞ ሳጥናኤል የሚቀናበት ክፉ ያደርጉሃል ። ከሰማሃቸው ደግሞ ራስህን የመሆን እድል አይሰጡህም ። ሁሉም በፈለጉት መንገድ ሊቀርፁህ መጥረቢያ ይስላሉ ። ልብህን ከከፈትክላቸው የየድርሻቸውን ጠርበው ቅርፅ አልባ ያደርጉሃል።

እኔና አንተ አንድ ቦታ ላይ በተለያየ አቅጣጫ ፊታችንን አዙረን ብንቆም የእኔ ቀኝ ያንተ ግራ ነው። 'ቀኝ ይሄ ነው ወይም ግራ ይሄ ነው' ብዬ ብከራከርህ ቂል ነኝ ። እንዳንተ አቋቋም ያንተ እውነት ይሆናል ። እንደ እኔ አቋቋም ደግሞ የእኔ እውነት ይሆናል ። ባንተ እውነት ለማመን ያንተን ጫማ መዋስ አለብኝ። የቆምኩበት ሆኜ ለስህተትህ ሒሳብ እየሰራሁ ስዳኝህ እቀሽማለሁ።


ጠበኛ እውነቶች
ሜሪ ፈለቀ

ውብ ቅዳሜ

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
2.2K views14:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 21:20:33
እውነትን ፣ቅንነትን ፣ ገንዘብ ከማድረግ በላይ ኮተትን ብቻ  ገንዘብ አድርጎ ህይወቱን በክህደት፣ በውሸት ፣በጥቅመኝነት ፣በአስመሳይነት በብልጣብልጥነት እየኖረ ኑሮ የበራለት የሚመስለው ሰውነት እንዴት ያልታደለ ነው።

የህሊና ፣ የቤተሰብ ሰላምና ደስታ በብልጣብልጥነት አይመጣም። ፈጣሪ ባህሪና ተግባራችንን ያያል። ከሰው የወሰድነውን ከሰውየው ብንደብቅ ከአምላክ አንደብቅም። የምናተርፈው ነገር ቢኖር የሆነ ጊዜ ላይ የሚመጣ መጥፎ ስቃይን ነው። ያውም ለልጅ የሚተርፍ የበደል ክፍያን ነው፣የቆምን መስሎን የዘነጋን…. ሰው የዘራውን ያጭዳልና እናስተውል።

መልካምነት ከማንም በላይ ላራስ ነው ጥቅምና ፍይዳው፣ ቅን ሀሳብ አሳቢውን ይባርካል። ከአንተ የመነጨና ተንደርድሮ የተተኮሰ ኃይል በእኩል መጠን እና ልክ አጥፊ እንደሆነ ሁሉ ራስህንም ያጠፍል፤ ሀሳብህን አልሚ ከአደረከው ደግሞ ቅድሚያ አንተን እና የእኔ የምትለውን ሁሉ ባርኮ ለሌሎች ይተርፋል።

መጥፎ ነገራችንን ሁሉ በመልካም ይቀየርልን

                              ሄለን ካሳ

ውብ አሁን

@EthioHumanity
@EthioHumanity
     
@EthioHumanitybot
2.0K views18:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 21:10:53 እኛ ሻማዎች ነን

<<...ባንድ ምሽት ሰውዬው በባሕር ዳርቻ ባለው የወደብ ከፍታ ቦታ ትንሽ ሻማ ይዞ መውጣት ይጀምራል። በዚህ ጊዜ 'ወዴት ነው እየሄድን ያለንው?' ሲል ሻማው ጥያቄ አቀረበለት።
"እየሄድን ያለነው ከቤቱ ባሻገር ከፍ ብሎ ወደሚታየው ቦታ ነው። በዚህም ለመርከቡ የወደቡን አቅጣጫ ማሳየት እንችላለን" አለው።
"እንደምታየው የእኔ ብርሃን በጣም ውስን ናት። እንዴትስ ከርቀት ያለ መርከብ በእኔ ብርሃን ተመርቶ ወደቡ ጋር መድረስ ይችላል?" አለ ሻማው።

"ምንም እንኳ ያንተ ብርሃን ትንሽ ብትሆንም የምትችለውን ያህል ማብራትህን አታቋርጥ፣ የቀረውን ነገር ለእኔ ተውው" አለው ሰውየው። በዚህ ንግግራቸው መሀል እያሉ ከከፍታ ቦታው ደረሱና ሰውዬው ትልቁን የፋኖስ ብርጭቆ እያሳየው ሻማውን በማስጠጋት ፋኖሱን ለኮሰው። ወዲያውኑም የተለኮሰው ፋኖስ የባሕሩን አካባቢ በብርሃን ጸዳል ሞላው።

እኛ ሻማዎች ነን። ከእኛ የሚጠበቀውም የሻማነታችንን ያህል ማብራት ነው። ቀሪው የሥራችን ስኬት ላይ ፈጣሪ ይታከልበታል። የአንዲት ትንሽ ሻማ መብራት ወይም ክብሪት ጫካ ሙሉ እሳት እንደምትፈጥር ሁሉ በእያንዳችን ያለች የብርሃን ምሳሌ ስናውቅም ሳናውቅም ለሌሎች ሕይወት መለወጥ ምክንያት ትሆናለችና ብርሃናችንን ሳንሳሳላት እንድትበራ እድል እንስጣት።

ዕድገትም ቅብብሎሽ ነው። እኛ ማድረግ የምንችለውን ሰርተን ለተገቢውና ለሚጠበቅብን ስናስረክበው እሱም በፈንታው ዳር ያደርሰዋል። ሻማዋ ለፋኖሱ እንዳቀበለችው ማለት ነው። ይህ ነው፣ ለዕድገት የድርሻን መወጣት ማለት፤ ሻማነታችንን ማበርከት የሚጠበቅብንን መወጣት። >>

እርካብና መንበር [ 117-118 ]
ዲራአዝ

ውብ  አዳር

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
1.6K viewsedited  18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 21:10:28
1.6K viewsedited  18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 21:20:20 ምክር  ለወዳጅ

ወዳጄ ሆይ!

ጨለማው ላይ ብታፈጥ ያለ ሰዓቱ አይነጋም።ፈጣሪህን ትተህ በመከራህ ላይ ብታፈጥ አንዳች ጥቅም የለውም።ካስተዋልከው ጨለማም ውበት አለው። ከካባ ይልቅ ደማቅ ነው። እሾህም አበባ አለው። ክፉ ሰውም አንድ ጥሩ ነገር አለው። ልብ አድርግ ለክረምት በጋ፤ ለሌሊት ቀን አለው። ላንተም ጊዜ አለህ። ጊዜን የሚሰጥ ራሱ ጊዜ ሳይሆን የጊዜ ባለቤት ፈጣሪ እንደሆነ እመንና ጠብቅ።

ወዳጄ ሆይ!!

አግኝቶ ያጣው ቶሎ ይከፋዋልና ታገሠው ። አጥቶ ያገኘ ምድር ይጠበዋልና ምክረው ። ከፍታህ ዝቅተኞችን በመርገጥ ፣ ህልውናህ በሌሎች ሬሳ ላይ አይሁን ። የፍቅር ሰው ለመባል ሁሉም ትክክል ነው አትበል ። ግልጽ ጥላቻ የፍቅር ያህል ነው ። ግልጽ ንግግር ሰሚውን ያከበረ ነው ። እጅግ ግልጽነትም የሚያስገምት ነው፣ ።የምሥጢር ሙዳይ ሁን እንጂ የእሳት ማንደጃ ወናፍ አትሁን ። ሰዎች ሊሰሙህ በሚችሉበት ችሎታቸውና ፍላጎታቸው መጠን ብቻ ተናገር ፣ ቁጥብ እንጂ ዝርው አትሁን ።


ወዳጄ ሆይ!

ለዕውቀት ትጋ ፣ በከፊል በተረዳኸው ነገር ራስክን እንደ አዋቂ አትቁጠር ። በከፊል ከማወቅ አለማወቅ ይሻላል ። "ሥራ ስትሠራ ደግሞ ነገ ትቼው ለምሞተው ወይም ብሠራ የሚጠቀመው ሌላ ነው" ፣ በሚል ተስፋ ቢስ ሆነህ ሳይሆን ዘላለም እንደምትኖር ያክል በመትጋት ነው ። ትጋት ጥሩ ነው ። ችኮላህ ግን ውጤት አያመጣም ፣በችኮላ መሥራትና በፍጥነት መሥራት የተለያዩ ናቸው ። እርኩሰት የዕውቀት እና ስልጣን መገለጫ አይደለምና ማንነትንና ሰብዓዊ ክብርን ከሚያጎድፉ ተግባራት መታቀብን ገንዘብ አድርግ ። "

እናም በየዕለቱ በኑሮህ ጠንቃቃ ሁን ። ያለጸጸት ነገን ለመኖር ዛሬን በቁም ነገር አሳልፍ ፤ ውሳኔዎችህ ትክክለኛ መሆናቸውን መርምር ፤ ልክ እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ወይም እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ደግመህ የምትኖረውንና ለማከናወን የምትመርጠውን ዐይነት ሕይወት ለመኖር ሞክር ።

             ውብ አሁን

@EthioHumanity
@EthioHumanity
     
@EthioHumanitybot
949 viewsedited  18:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 21:19:42
931 views18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 18:39:05 መዝራትና ማጨድ

“እያንዳንዱ ቀንህን መመዘን ያለብህ በሰበሰብከው ፍሬ ሳይሆን በዘራኸውና በተከልከው ዘር ነው” - Robert Louis Stevenson

ሁሉም ነገር የሚፈጠረው ሁለት ጊዜ ነው፣ በመጀመሪያ በሃሳብ መልክ፣ ከዚያም በገሃዱ ዓለም፡፡ ዛሬ በሃሳብ፣ በንግግርም ሆነ በተግባር የሚዘራው ዘር የነገውን እውነታ እንደሚፈጥርበት የማያስተውል ግለሰብም ሆነ ሕብረተሰብ ጥበብ እንደጎደለው ማሰብ አያስቸግርም፡፡ ይህንን የመዝራትና የማጨድ ሕግ ያልተገነዘበና ስርአት የሌለው ሕብረተሰብ በውጤቱ ለአመለካከቱና ለራሱ የሚገባውንና የሚመጥነውን አለም ይፈጥራል፡፡

የምትኖርበት ሕብረተሰብ ያለበትን የወቅቱን ሁኔታ ተመልከት፡፡ ይህ ሕብረተሰብህ ያንን ሁኔታ ማንም አልፈጠረበትም፤ ቢፈጥርበትም ያንን ተቀብሎ የመኖርን ደካማነት ማንም አላስታቀፈውም፡፡ ይህ ሕብረተሰብ ትናንት የዘራውን ዘር ፍሬ ዛሬ እየበላ ነው፡፡ ይህ እውነታ ደግሞ በዙሪያችንም ሆነ በግል ሕይወታችን የምናያቸውን መልካምም ሆነ ክፉ ሁኔታዎች የሚወክል የማይለወጥ እውነታ ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ፣ እንደ ግለሰብም ሆነ እንደ ማሕበረሰብ የምንኖርበትን ዓለም የምንፈጥረው እኛው ራሳችን ነን፡፡    

አንድ ሕብረተሰብ ከጥበብ ጎዳና ሲርቅ፣ ትናንት ያቆሸሸው አካባቢ ዛሬ በስብሶ ነገ በሽታን እንደሚሰጠው ማሰብ ያቅተዋል፡፡ ይህ አይነቱ ህብረተሰብ ባለበት ሲርመሰመስና የራሱን ቁስል በራሱ ምርጫና ውሳኔ ሲፈጥር አመታትን ያሳልፋል፡፡ ዛሬ በራስ ወዳድነት፣ በእኔ እበልጣለሁ ስሜትና በስግብግብነት የጎዳው የሕብረተሰብ ክፍል ነገ መልሶ ያንኑ ዛሬ እርሱ የዘራውን ዘር ፍሬ ጨምቆ መራራ ጽዋ እንደሚያስጎነጨው አያስተውለውም፡፡ በከፍታ ዘመኑ ለሰዎች ግድ-የለሽነት የዘራ ጥበብ-የለሽ ሰው፣ የእርሱ ዘመን አልፎ የሌላው ዘመን ሲመጣ ከእርሱ የባሱ ግድ-የለሾች እንዲፈጠሩ የሚያደርገው እርሱው ራሱ መሆኑን መዘንጋት የለበትም፡፡

የዛሬ ጉልበተኛ፣ ነገ ከእርሱ በኋላ የሚነሳው የዘመኑ ጉልበተኛ እንዲረግጠው የሚያደርግን ዓለም የሚፈጥረው ራሱው ነው፡፡ ይህንን ሕብረተሰቡ ከዘመን ወደ ዘመን ሲርመሰመስ የሚኖርበትን ኡደት ግን ለመስበር አቅም ያለው ሰው የጥበብን መንገድ ለማስተዋል ራሱን የሰጠ ሰው ብቻ ነው፡፡  

በጤንነት ዘመንህ ጊዜ ያልዘራኸውን በሕመም ጊዜ አታገኘውም፣ ያልተዘራው አይበቅልምና! በወጣትነት ጊዜ ያልዘራኸውን በሽምግልናህ ዘመን አታገኘውም፣ በሽምግልና ዘመን የሚበላው በወጣትነት ዘመን የተዘራው ዘር ነውና፡፡፡ በብዙ ወዳጅ በተከበብክና በተወዳጅነትህ ጊዜ ያልዘራኸውን በብቸኝነት ጊዜ አታገኘውም፡፡ በአመራር ከፍታ ዘመንህ ያልዘራኸውን የአመራር ዘመንህ ሲያልፍ (ማለፉ አይቀርምና) አታገኘውም፡፡  ከዚህ ውጪ ስሌት የለም፡፡ 

በሚገባ ስናስበው ምርጫችን እጅግ ውስን ነው፡፡ አንዱ ምርጫችን ጤና-ቢሱን ዘር ዘርተን ጤና-ቢሱን ፍሬ ሲበሉ መኖር፡፡ ሌላኛው ምርጫችን፣ የነገን በማሰብ ዛሬ መልካም ዘርን በመዝራት የነገውን ፍሬያችንን በቁጥጥር ስር ማዋል ነው፡፡ ከእነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት ምርጫዎች ለየት ያለውን ምርጫ የሚከተሉ ብዙ ሰዎች፣ በጠማማ መንገድ ረጅም ርቀት ከተጓዙና በመጨረሻ ሁሉን ነገር ካጡ በኋላ ትክክለኛውን ነገር ፍለጋ ወደኋላ ይመለሳሉ፡፡ በንግግራቸውና በተግባራቸው የማይሆንን ዘር ሲዘሩ ከርመው አረምን ሲለቅሙ የመኖር ሞኝነት፡፡

መፍትሄው አጭርና ግልጽ ነው፡፡ የምትበላውን ፍሬ ካልወደድከው፣ የዘራኸውን ዘር አስተውልና ቀይረው፡፡ ዘርህ ሲቀየር ፍሬውም ከዚያው ጋር ይለወጣል፡፡ ዛሬ  በምትወስነው ውሳኔህ፣ በምትመርጠው ምርጫህና በምትዘራው ዘርህ የነገህን በትክክል መተንበይ ትችላለህ፡፡

ውብ ቅዳሜ!

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
1.5K viewsedited  15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 18:38:52
1.4K views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ