Get Mystery Box with random crypto!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የሰርጥ አድራሻ: @ethiobooks
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.34K
የሰርጥ መግለጫ

✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል!
የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ።
ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ
@firaolbm እና
@tekletsadikK ተጠቀሙ።

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2023-03-10 08:05:20
202 viewsተስፋዬ መብራቱ, 05:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 10:53:40 ፎቢያ (Phobia)
━━ ✦ ━━

ፎቢያ መጠነኛ ወይም ምንም ጉዳት ለማያመጡ ነገሮች ከመጠን ያለፈና ምክንያት የለሽ ፍራቻ ሲሆን፤ በዚህ የተነሳ ጭንቀትና ያንን ፍራቻ ለመሸሽ የመፈለግ ስሜት ነው። ፎቢያ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ፣ አካላዊና ስነ-ልቡናዊ ምላሽ ያለውና በሥራ ቦታ እንዲሁም በማህበራዊ መስተጋብር ላይ ችግር ሊፈጥር የሚችል የፍራቻ ስሜት ነው።

የፎቢያ አይነቶች ብዙ ናቸው። ጥቂቶቹን ለመመልከት ያህል፦

ኤሮፎቢያ ➥ በአውሮፕላን የመብረር ፍርሃት

ኒክቶፎቢያ ➥ የጨለማ ፍርሃት

አክሮፎቢያ ➥ የከፍታ ቦታዎች ፍርሃት

ታላሶፎቢያ ➥ ትላልቅ የውሃ አካላት ከመጠን በላይ መፍራት

አማክሶፎቢያ ➥ ተሽከርካሪ የመንዳት ፍርሃት

ሄማቶፎቢያ ➥ ደም፣ ቁስሎች እና ከነሱ ጋር የተያያዙ ነገሮች ለምሳሌ መርፌዎች፣ ፍርሃት

ክላስትሮፎቢያ ➥ የተዘጉ፣ የተከለከሉ፣ የታሸጉ ቦታዎች፣ የአሳንሰር ወዘተ ፍራቻ

ታናቶፎቢያ ➥ ሞትን መፍራት

ብሮንቶፎቢያ ➥ የነጎድጓድ፣ የመብረቅ፣ የማዕበል እና የመሳሰሉት ፍራቻ

ፊሎፎቢያ ➥ በፍቅር የመውደቅ ፍርሃት

ግሎሶፎቢያ ➥ የአደባባይ ንግግር ፍርሃት

ኖሞፎቢያ ➥ ያለ ሞባይል ስልክ የመሆን ፍርሃት

ጌራስኮፎቢያ ➥ የእርጅና ፍርሃት

አብሉቶፎቢያ ➥ ገላን የመታጠብ ፍርሃት

ድሮሞፎቢያ ➥ መንገድ የመሻገር ፍርሃት

ጋሞፎቢያ ➥ የጋብቻ ፍራቻ

ዩሮፎቢያ ➥ የሽንት መሽናት ፍርሃት

ሳይቶፎቢያ ➥ የምግብ ፍርሃት

አውቶማይሳ ፎቢያ ➥ ንጹህ ያለመሆን ፍርሃት

ሃይድሮ ፎቢያ ➥ የውሃ ፍራቻ

አውቶፎቢያ ➥ ብቻ የመሆን ፍራቻ

እና ሌሎች በርካታ የፎቢያ ወይም የፍራቻ ዓይነቶች አሉ።

ሁሉም ፎቢያዎች ህክምና ላያስፈልጋቸው ይችላል። ነገር ግን ምክንያት የሌለው ከመጠን ያለፈ ፍራቻ (ፎቢያ) ካለና፤ በዚህም ምክንያት በሥራና ማህበራዊ ግንኙነት ላይ ጫና ከተፈጠረ የህክምና ወይም የስነልቦና አገልግሎት ማግኘት ይመከራል።
━━━━━━━━

https://t.me/Ethiobooks
536 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 10:00:11 አበራ ለማ የተወለደው በ1943 ዓ.ም. ፍቼ
ሰላሌ ውስጥ ነው። እድገቱ ወሊሶንና አዲስ አበባን ያካትታል። ካገራችን ገጣሚያንና አጫጭር ልቦለድ ጸሓፊዎች አንዱ ነው። በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሑፍ ጥናት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማዕርግ ተመራቂ ነው። ሙያው ጋዜጠኝነት ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ሬዲዮና ፕሬስ መምሪያዎች ሠርቷል። ከጦር
ግምባር ጋዜጠኝነት እስከ ኪነጥበባት ዘርፎች ሃያሲነት ዘልቋል።

እስከ ሰማኒያዎቹ አሠርት አጋማሽ ድረስ፥
የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር ዋና ጸሃፊ ሆኖ አገልግሏል። ዛሬ የኖርዌይ ነዋሪ ነው።
በኖርዌይ ደራስያን ማኅበር ብቸኛውና
የመጀመሪያው ጥቁርና በአፍ መፍቻ ቋንቋው የሚጽፍ አባል ደራሲ ነው።

በዚህ ማኅበር ውስጥ የዓለም አቀፍ ኮሚቴው የረዥም ዘመን አባል በመሆንም ይታወቃል። ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድህንን በ1997 እ.ኤ.አ.፣ ስዊድናዊ/ኤርትራዊ የሆነውን የአስመራውን እስረኛ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሐቅን በ2009 እ.ኤ.አ. ሃሳብን በነጻ የመግለጽ ሽልማት እንዲሸለሙ በእጩነት አቅርቦ ማሸለሙም ይታወሳል።

ከአበራ ለማ የታተሙ ሥራዎች፦
➦ ኩል ወይስ ጥላሸት፣ የግጥም መድብል 1967
➦ ሽበት፣ የግጥም መድብል 1974
➦ ሕይወትና ሞት፣ የአጫጭር ልብ ወለዶች መድብል 1975
➦ ሞገደኛው ነውጤ፣ 1976 ኖቭሌት
➦ አባደፋር፣ ከሌሎች ደራስያን ጋር ስብስብ 1978
➦ ጽጌረዳ ብዕር፣ ከሌሎች ገጣሚያን ጋር ስብስብ 1978
➦ የማለዳ ስንቅ፣ ያጫጭር ልቦለዶችና ግጥሞች መድብል 1980
➦ መቆያ፣ ያጫጭር ልቦለዶችና ግጥሞች መድብል 1980
➦ ትዝታን በጸጸት፣ ያጫጭር ልቦለዶች ትርጉም (በጋራ) 1981
➦ አውጫጭኝ፣ የግጥም መድብል 1994
➦ ሙያዊ ሙዳዬ ቃላት፣ ኢልቦለድ 1994
➦ የእውቀት ማኅደር፣ ኢልቦለድ 1998
➦ እውነትም እኛ፣ የግጥሞች ስብስብ ቪዲዮ በዲቪዲ፣ ታህሳስ 2003
➦ ጥሎ ማለፍ፣ ታሪካዊ ልቦለድ
➦ ሽፈራው ሞሪንጋ ጥር 2003
➦ ቅንጣት - የኔዎቹ ኖቭሌቶች 2008
➦ ኩርፊያና ፈገግታ፣ የግጥም መድብል 2013
➦ የኢትዮጵያውያን ገጣሚያን ሥራዎች ወደ ራሽያ ቋንቋ የተተረጎመ በጋራ 1981 G.C.
➦ ULIKE HORISONTER - (ኖርዌጂያንኛ ግጥሞች) በጋራ 2003 G.C.
➦ ENKETRØSTREN (በኖርዌጂያን ኖቭሌቶች) 2017 G.C.
➦ TIME TO SAY NO፣ (የእንግሊዝኛ ግጥሞች) በጋራ 2014 G.C.
➦ ትውስብ - ያጫጭር ልቦለዶችና ኖቭሌቶች ስብስብ 2014 ፤ ይጠቀሳሉ።

ደራሲ አበራ ለማ በ2013 ዓ.ም. ሁለት ከፍተኛ ሽልማቶችን በኢትዮጵያ አግኝቷል፡፡ እነርሱም፦
1. ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ በ2013 ዓ.ም. የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ምርጥ ጋዜጠኛ
2. የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር የክብር ሜዳይ ሽልማት፣ በሥነ ጽሑፍ አስተዋጽኦ፣ 2013 ዓ.ም. ናቸው።
━━━━━━━
ዊኪፒዲያ

https://t.me/Ethiobooks
450 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 09:56:24
--- ደ ራ ሲ አ በ ራ ለ ማ ---
424 viewsተስፋዬ መብራቱ, 06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 11:30:05 የዓድዋ ጦርነት ትዝታ - 2 የመጨረሻው!
386 viewsተስፋዬ መብራቱ, 08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 11:00:21 የዓድዋ ጦርነት ትዝታ - 1
423 viewsተስፋዬ መብራቱ, 08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 10:58:27
የፊታውራሪ ተ/ሐዋርያት ተ/ማርያም
የዓድዋ ጦርነት ትዝታ
━━━━━━━
@ethiobooks
436 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 10:58:12
405 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 09:14:53
ዋ! . . . ያቺ አድዋ
  ══✦══
ፀጋዬ ገብረ መድኅን
'
ዓድዋ ሩቅዋ
የዓለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ
ዓድዋ . . . . .
ባንቺ ብቻ ህልውና
በትዝታሽ ብፅዕና
በመስዋዕት ክንድሽ ዜና
አበው ታደሙ እንደገና . . . .

ዋ !
ዓድዋ የዘር ዐፅመ ርስትዋ
የደም ትቢያ መቀነትዋ
በሞት ከባርነት ሥርየት
በደም ለነፃነት ስለት
አበው የተሰውብሽ ለት ፤
ዓድዋ
የኩሩ ትውልድ ቅርስዋ
የኢትዮጲያዊነት ምስክርዋ
ዓድዋ
የኩሩ ደም ባንቺ ጽዋ
ታድማ በመዘንበልዋ
ዐፅምሽ በትንሳኤ ነፋስ
ደምሽ በነፃነት ሕዋስ
ሲቀሰቀስ ትንሳኤዋ
ተግ ሲል ሲንር ጥሪዋ
ድው - እልም ሲል ጋሻዋ
ሲያስተጋባ ከበሮዋ
ሲያስገመግም ዳኘው መድፍዋ
ያባ መቻል ያባ ዳኘው
ያባ ነፍሶ ያባ ቃኘው
ያባ በለው በለው ሲለው
በለው - በለው - በለው - በለው !

ዋ ! . . . . ዓድዋ . . . .
ያንቺን ጽዋ ያንቺን አይጣል
ማስቻል ያለው አባ መቻል
በዳኘው ልብ በአባ መላው
በገበየሁ በአባ ጎራው
በአባ ነፍሶ በአባ ቃኘው
በለው ብሎ ፥ በለው - በለው !

ዋ ! . . . . ዓድዋ . . . .
ዓድዋ የትላንትዋ
ይኸው ባንቺ ህልውና
በትዝታሽ ብፅዕና
በመስዋዕት ክንድሽ ዝና
በነፃነት ቅርስሽ ዜና
አበው ተነሱ እንደገና ።

. . . . . ዋ ! . . . . .ያቺ ዓድዋ
ዓድዋ ሩቅዋ
የአለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ
ዓድዋ . . . . .
════════
የካቲት - ፲፱፻፷፬ - ዓድዋ

https://t.me/Ethiobooks
419 viewsተስፋዬ መብራቱ, 06:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 13:20:57 የአድዋ ጦርነት
━━✦━━

የአድዋ ጦርነት በ1888 ዓመተ ምሕረት በየካቲት 23 ቀን እሑድ ተዠመረ፡፡ ወዲያው የኢጣሊያ የጦር አዛዥ ያገር ተወላጅን ጦር እፊት አስቀድሞ ሲዋጋ በኋላ የራስ መንገሻና የራስ ሚካኤል የዋግ ሥዩም ጓንጉል ወታደሮች ከበው በጥይት ስለ ቆሏቸው ይበልጦቹ እጦርነቱ ላይ ሞቱ፡፡ ገሚሶቹ ዐውቀው እጃቸውን ሲሰጡ የቀሩት ደግሞ ወዳልተነካው ጦር ወደ ጄኔራል አርሞንዲ ሠራዊት በሽሽት እየሄዱ ተደባለቁ፡፡

የኢትዮጵያ የጦር ሠራዊትም እያቅራራና እየፎከረ ወደ ፊት አልፎ ጎስሶ ከሚባለው ጉብታ ላይ ደርሶ እንደገና ተጋጠማቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ዠግናው ፊታውራሪ ገበየሁ ከሠራዊታቸው ተለይተው እጠላት መካከል ገብተው ከቀኛዝማች ታፈሰ ጋራ እየፎከሩ የጠላትን አንገት በጎራዴ ሲቆርጡ በጥይት ተመተው ወደቁ፡፡

ንጉሠ ነገሥቱ ዐፄ ምኒልክ የጦር ወታደራቸውን በሚያበረታታ ቃል ሲያደፋፍሩ እንዲሁም እቴጌ ጣይቱ እንደ ወንድ በጦርነቱ መካከል እየተላለፉ የቆሰለውን ሲያነሱ ለተጠማው መጠጥ ለተራበው ምግብ ሲያሰጡ ዋሉ፡፡ እነ ሊቀ መኳስ አባተ እነ ራስ አሉላ እነ በጅሮንድ ባልቻ እነ ደጃች በሻኽ አቦዬና የቀሩትም የጥንት ወታደሮች በመድፍና በጠመንዣ በዠግንነት ሲዋጉ የጠመንዣውና የመድፉ ጩኸት ከልክ ያለፈ ነበር፡፡

የኢጣሊያንንም ወታደር ከበው እየተፏከሩ በጥይትና በጎራዴ ሲደበድቡት የኢጣሊያ ጦር በዠግንነት አራት ሰዓት ከተዋጋ በኋላ ሽሽት ዠመረ፡፡ በዚህ ጊዜ ኢትዮጵያውያን እየተከታተሉ ሲወጉት አዝማቹ ጄኔራል አልቤርቶኒ ተቀምጦበት የነበረው በቅሎ ተመቶ ወደቀ፡፡ ኢትዮጵያውያን ደርሰውም ጄኔራሉን ማረኩት፡፡

የአንደኛው ክፍል ጦር አዛዡ ተማርኮ ሠራዊቱ በጭራሽ ከጠፋ በኋላ ሁለተኛው ክፍል የጦር ሠራዊት ራአዮ ከሚባለው ስፍራ ላይ ሆኖ ካራት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ የሦስተኛውን ክፍል የጄኔራል ኤሌናን ጦር ጨምሮ ተዋግቶ በመጨረሻ የጦር አዛዡ ጄኔራል አሪሞንዲ እዚያው እጦርነቱ ላይ ሞቶ ተገኘ፡፡ ከዚህም በኋላ በመጨረሻ ያለው የኢጣሊያ ጦር በተለይ ማርያም ሸዊቶ ከሚባለው ስፍራ ላይ ተጋጥሞ ከቀድሞው የበለጠ ጦርነት ተደረገ፡፡

ይልቁንም የመጨረሻው ድል የሚፈጸምበት ለመሆኑ የሁለቱም የጦር ሠራዊት ተደባልቆ በጨበጣ በሚዋጉበት ጊዜ በጨበጣ በሚደረገው ዘመቻ ከኢጣሊያኖች ይልቅ ኢትዮጵያውያን በጎራዴ አነዛዘር የቀለጠፉ ነበሩ፡፡ በዚህ ጊዜ ኢጣሊያኖች ገሚሶቹ ሲሞቱ የቀሩት ደግሞ ወደ ኢትዮጵያውያን ደግነው ይተኩሱበት የነበረውን ብረት አፈሙዙን ጨብጠው ሰደፉን ወደ ሰማይ እየሰቀሉ ተማረኩ፡፡

ድሉም በማያወላውል አኳኋን የኢትዮጵያ ሆኖ ጦርነቱ በ1888 ዓመተ ምሕረት በዚህ በየካቲት 23 ቀን ተፈጸመ፡፡
━━━━━━━━
ተክለ ጻዲቅ መኲሪያ
የኢትዮጵያ ታሪክ ከአፄ ቴዎድሮስ
እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ

https://t.me/Ethiobooks
461 viewsተስፋዬ መብራቱ, 10:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ