2023-06-06 10:36:00
2 ጢሞቴዎስ 3 ፥10_14
10፤ አንተ ግን ትምህርቴንና አካሄዴን አሳቤንም እምነቴንም ትዕግሥቴንም ፍቅሬንም መጽናቴንም ስደቴንም መከራዬንም ተከተልህ፤
11፤ በአንጾኪያና በኢቆንዮን በልስጥራንም የሆነብኝን የታገሥሁትንም ስደት ታውቃለህ፤ ጌታም ከሁሉ አዳነኝ።
12፤ በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ።
13፤ ነገር ግን ክፉዎች ሰዎችና አታላዮች፥ እያሳቱና እየሳቱ፥ በክፋት እየባሱ ይሄዳሉ።
14፤ አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤
ይህ ሕዝባችንን ሲያጣምም ለቄሣርም ግብር እንዳይሰጥ ሲከለክል ደግሞም፡— እኔ ክርስቶስ ንጉሥ ነኝ፡ ሲል አገኘነው፡ ብለው ይከሱት ጀመር።
ሉቃ 23፥2
15፤ ስለዚህ ፈሪሳውያን ሄዱና እንዴት አድርገው በነገር እንዲያጠምዱት ተማከሩ።
16፤ ደቀ መዛሙርታቸውንም ከሄሮድስ ወገን ጋር ላኩበት፥ እነርሱም፡— መምህር ሆይ፥ እውነተኛ እንደ ሆንህ በእውነትም የእግዚአብሔርን መንገድ እንድታስተምር እናውቃለን፥ ለማንምም አታደላም፥ የሰውን ፊት አትመለከትምና፤
17፤ እንግዲህ ምን ይመስልሃል? ንገረን ለቄሣር ግብር መስጠት ተፈቅዶአልን ወይስ አልተፈቀደም? አሉት።
18፤ ኢየሱስም ክፋታቸውን አውቆ፡— እናንተ ግብዞች፥ ስለ ምን ትፈትኑኛላችሁ?
19፤ የግብሩን ብር አሳዩኝ፡ አለ። እነርሱም ዲናር አመጡለት።
20፤ እርሱም፡— ይህች መልክ ጽሕፈቲቱስ የማን ናት? አላቸው።
21፤ የቄሣር ነው፡ አሉት። በዚያን ጊዜ፡— እንኪያስ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር አስረክቡ፡ አላቸው።
22፤ ይህንም ሰምተው ተደነቁ፥ ትተውትም ሄዱ።
ማቴ 22፥15_22
እነዚህ የእግዚአብሔር ቃሎች
እንደሚያስረዱን
ሀ _ በንስሓ በእውነት በእምነት ከክፋት በመራቅ እውነተኛ በመሆን እግዚአብሔርን ሊመስል የሚወድ ሁሉ ይሰደዳል።በማን ?እውነትን በሚጠሉ
እግዚአብሔርን መምሰል የሚፈልገውም ምርጫ ነውና በሚደርሰበት ሁሉ ደስተኛ ነው።።
ለ_,እግዚአብሔርን መምሰል የሚፈልግ ሰው ሲከሰስ ደግሞ በሀሰት ነው። ከቃሉ እንደምናየው ኢየሱስ ክርስቶስን በነገር ሊያጠምዱት በፈለጉ ጊዜ ለቄሣር ግብር መስጠት ተፈቅዷልን ?ወይስ አልተፈቀም ብለው በጠየቁት ጊዜ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር አስረክቡ አለ እንጂ!!ለቄሣር ግብር አትስጡ አላለም።
ሲከሱት ግን ለቄሣር ግብር እንዳይሰጥ ሲከለክል ንጉስነኝም ሲል ሕዝቡንም ሲያጣምም አገኘነው ብለው ከሰሱት። ከክሶቹ ውስጥ አንድም እውነት የለም።
ሕዝቡን አጣመመ የተባለው እናንተ ግብዞች እናንተ በኖራ የተለሰነ መቃብር የምትመስሉ እናተም ወደ እግዚአብሔር መንግስት አትገቡም ሌሎትም እንዳይገቡ ትከልክላላችሁ እያለ ስለገሰጻቸው ሕዝቡን ያጣምማል እያሉ ከሰሱት። ንጉሱ ጨክኖ እንዲያጠፋላቸው ንጉስ ነኝ ሲል አገኘው ግብርም እንዳይሰኝጥ ሲከለክል አገኘነው ብለው ከሰሱት።
ግን ዛሬ ላይ ሁሉም ክስ ውሸት ብቻ ነው።
ዛሬም የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስለ ገሰጻቸው በሀሰት ይከሱታል የመልእክቱን ተግሳጽ ሰምተን የእግዚአብሔር መልእክት ነው ብለን ስለተቀበልን ያሳድዱናል። ግን ምርጫችን ስለሆነ ደስስ ይለናል እንጂ አይከፋንም።
እናም ውድ የእግዚአብሔር ሕዝቦች እንቁ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች ። እግዚአብሔርን መምሰል ምርጫችን እስካደረግን ድረስ በደጉም በክፉም ነገር ሁሉ ደስተኞች ልሆን ይገባል። በእኛ ሕይወት ላይ እግዚአብሔር ሳይፈቅድ ጠላት አንዲት ነገር ማድረግ እንደማይችል ተምረናልና።
አባትችን ቸሩ መድኃኔ ዓለም ከፈቀደ ደግሞ ሁሉም ይሁን። ምክንያቱም ምርጫችን ያደረግነው እግዚአብሔር ለሕይወታችን የመረጠልንን በደስታ ስንቀበል እንደ ኢዮብ ያስመሰግናልና።
በሆነው ባልሆነውም በሚሆነው ሁሉ ግን የድግል ማርያም ልጅ የቅዱሳን አምላክ ቸሩ መድኃኔ ዓለም የተመሰገነ ይሁን ።አሜን።
128 views07:36