Get Mystery Box with random crypto!

እንደዛሬ የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ውስጤ እረክቶ አያውቅም፡፡ ፡፡፡ ፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ | የኤፍሬም እይታዎች (መ/ር)

እንደዛሬ የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ውስጤ እረክቶ አያውቅም፡፡
፡፡፡ ፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ዋናው መልእክት
የ EOTC ሲኖዶስ በሰጠው መግለጫ ጥጠሚ አብይ አህመድ ትላንት ለካቢኔው የተናገራቸውን ስህተቶች አንድ በአንድ ነቅሶ አውጥቷል::

ዋና ዋናዎቹ ነጥቦች:-

1- ህገወጡን ሲኖዶስ ከህጋዊው ሲኖዶስ ጋር አቻ አድርጎ ማቅረብ
- ስህተት

2- ጉዳዩ ቀላል በድርድር የሚፈታ ነው ያለው
(ከባድ ቀኖናዊ ጥሰት በመኾነኑ)
- ስህተት

3- ሁለት ፓትርያርክ ሃገር ላይ ነበር ያለው
- ውሸት

4- ትግራይ ጳጳስ ተሹሞ ፣ ሲኖዶስ ተቋቁሞ ነበር ያለው
- ውሸት

5 - ባለፈው 4ዓመት ለ EOTC ተሰጠ ያለው መሬት - (ቤ/ክ already በስሯ ላሉ ለይዞታዋ ህጋዊ ካርታ ነው የወሰደችው)
- ውሸት

6- ጠ/ሚው በግልፅ ለህገወጡ ስብስብ ድጋፍ ማሳየቱ ፣ መንግስት ህጋዊ እውቅና ላለው የቤ/ክ ሲኖዶስ ህግ በማስከበር መተባበር ሲገባው .. በተቃራኒ ቆሞ ህገወጦችን ማገዙ ፣ አባቶችን ማዋከብ ና ማሰሩ
- ህገወጥ

7- በቋንቋ መጠቀምን በተመለከተ ቤ/ክ ላይ ያቀረበው ክስ .. በኦሮምኛ ቋንቋ መገልገል ብቻ ሳይኾን መፅሃፍትም እንደታተሙ ፣ መንፈሳዊ ኮሌጆችም እደተከፈቱ ፣ ህገወጥ ተግባር ላይ ያሉትም ሰዎች በዚችው ቤ/ክ የተሾሙ እንደነበሩ በመጥቀስ
- ውሸት እንደኾነ አሳይቷል::