Get Mystery Box with random crypto!

Edris Zulbijadeyn

የቴሌግራም ቻናል አርማ edriszulbijadeyn — Edris Zulbijadeyn E
የቴሌግራም ቻናል አርማ edriszulbijadeyn — Edris Zulbijadeyn
የሰርጥ አድራሻ: @edriszulbijadeyn
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 279
የሰርጥ መግለጫ

بداية خير
بداية جديدة مع الله
بداية لا يأس فيها
بداية جميلة بأذن الله 🧡🤲🏻
هذي القناة صدقه جاريه ...

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2022-05-28 19:26:52 Ahmedin Jebel - አሕመዲን ጀበል:
«አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም።»


ሙፍቲ ሐጅ ዑመር እድሪስ አልፎ አልፎ ሚዲያ ባለበት ሕዝባዊ ስብሰባዎችም ሆነ መግለጫ ላይ ከሚያነሷቸው ነጥቦች አንዱ ስልጣንና ዱንያዊ ጥቅማ ጥቅምን እንደማይፈልጉ የሚገልጹባቸው ቃላቶች ይገኙባቸዋል። የዱንያዊው ጥቅም ጉዳይ ለጊዜው በይደር ይቆየኝና ስልጣን እንደማይፈልጉ ከሚገልጹባቸው መካከል «አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም» ከሚለው ጋር በተያያዘ ጥቂት ልበል።

በቅርበት የማያውቃቸው ሰው "ታዲያ ስልጣን የማይፈልጉ ከሆነ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) በይፋ ከተመሠረተበት እስከ ዛሬ (ከመጋቢት 4 ቀን 1968 እስከ 2014 ግንቦት) መንግስታት ሲቀያየሩ ጭምር ቦታ እየቀያየሩና እየተመሳሰሉ እንዴት መጅሊስ ዉስጥ ለ46 ዓመታት በስልጣን ላይ መቆየት ቻሉ?" የሚል ጥያቄ በአዕምሮው ሊያጭርበት ይችላል።

ሙፍቲ የመጅሊስ ምርጫ ጉዳይ ሲነሳ ምርጫ ከተደረገ ከስልጣን እንደሚለቁ ስለሚያውቁ አጀንዳውን ለማዳፈን በተደጋጋሚ የሚያቀርቡት ማስፈራሪያ ከመጅሊስ ስልጣን ከተነሱ «መጅሊስ ለሁለት ይከፈላል» የሚለው ዛቻ ነው። ለሁለት ሲከፈል እሳቸው የአንዱ ክፋይ መሪ ሆነው እንዲቀጥሉ ሲባል ማለት ነው።

መጀመሪያ ዑለሞችና የቦርድ አባላት ሲመረጡ የመጅሊስ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ። ለስድስት ወራት በተባለው የሽግግር ጊዜ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ሳይወጡ 3 ዓመት አለፋቸው። ቆይተው ደግሞ በግልጽና በይፋ የተሰጠ ኃላፊነት ሆኖ ሳለ አንዴ «ስድስት ወር ብሎ ነገር የለም። ቋሚ ነን»፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ «እንደ ፓትሪያርኩ አንዴ ተመርጫለሁ እስከ ሕይወት ፍጻሜ ድረስ አልወርድም» ማለት ጀመሩ።

በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ ሥር የመጅሊስ መተዳደሪያ ደንብን እንዲያዘጋጅ ተሰይሞ የነበረው የነበረው ኮሚቴ መተዳደሪያ ደንቡን ለዋናው ኮሚቴው ሲያቀርብ የሚመረጠው ዋና ሙፍቲ በንቃት ሕዝበ ሙስሊሙን ለማገልገል እንዲችል «እድሜው ከ40 ያላነሰና ከሰማንያ ያልበለጠ» የሚለው ነጥብ ሲጠቀስ ከሐጅ ዑመር ተቃውሞ ገጠመው። «ከሰማንያ ያልበለጠ የሚለው የእድሜ ገደቡ ይነሳ» አሉ። ይህም ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ መሆኑ ግልጽ ነው።

ቀጥሎም ሌላኛው መስፈርት «ዐረብኛ ቋንቋ መናገር፣ መጻፍና ማንበብ መቻል አለበት» የሚለው ነጥብ ጋር ሲደረስም «የሀገራችን ብዙ ዑለሞች ዐረብኛ መናገር ስለማይችሉ የዐረብኛ ቋንቋ መስፈርቱ ይቅር» ብለው ተቃወሙ። በኋላ ስረዳ እሳቸው «ይህ መስፈርት እኔ እንዳልመረጥ ሆነ ብላችሁ ያስገባችሁት ነው» ብለው መተዳደሪያ ደንቡን በአሉታዊ ጎኑ ማየት መጀመራቸውን ተረዳሁ።

ለስድስት ወራት ከ26 ዑለማና ቦርድ ጋር የጊዜያዊ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲሾሙም አንዱ በጊዜው እንዲሰሩ በይፋ የተቀመጠው በባለሞያዎች የተዘጋጀው ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ተጨማሪ ዉይይት በማድረግ ማፅደቅ ቢሆንም ባለፉት 3 ዓመታት አንዴ እንኳን ዞር ተብሎ ሳይታይ ያ መተዳደሪያ ደንብ ተትቶ ሌላ ተዘጋጅቶ በቅርብ ጊዜ ለውይይት ቀረበ።በእርሳቸው መሪነትም ዉይይት ተደረገበት።በመጨረሻም በአብላጫ ድምፅ ጸደቀ።

መጅሊስ በ1968 ሲመሠረት በመተዳደሪያ ደንቡ ምርጫ እንደሚደረግ በግልጽ እንደሚደነግግ የሚያውቁና መተዳደሪያ ደንቡ ላይ የፈረሙ፣ በተደጋጋሚ ጊዜም በመጅሊስ ምርጫ ላይ የተሳተፉ ነበሩ። ሌላው ቀርቶ በ2005 ሕዝበ ሙስሊሙ በፌደራል ጉዳይ አማካኝነት በየቀበሌ ተደረገ በተባለው ምርጫ እንኳን በመራጭም ሆነ በተመራጭነት የተሳተፉ ነበሩ። ሆኖም እርሳቸው ለጊዜያዊነት ተብሎ ለስድስት ወር የመጅሊስ ፕሬዝዳንት ሲሆኑ ከቦታው ላለመነሳት አንዴ «በእስልምና ምርጫ የለም» ሲሉ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ «የክርስቲያኖች ፓትሪያርክ አንዴ ከተመረጠ በሕይወት እስካለ ሌላ ምርጫ አይደረግም። የኛም እንደዚህ ቢሆን ጥሩ ነው» የሚል ሐሳብ አመጡ። ይህም ተቀባይነት ሲያጣ በሕዝባዊ ምርጫ እሳቸው መሪ ሆነው እንደማይመረጡ ሲረዱ «ዑለማ ዑለማን ይመርጣል እንጂ ሕዝቡ ምርጫው አይመለከተውም፞። የሚመርጡትን ዑለሞች ደግሞ እኛ እንመርጣቸዋለን። የመረጥናቸው ዑለሞች ደግሞ መሪዎቻቸውን ይመርጣሉ» የሚል አቋም አራመዱ።

ሐጅ ዑመር እድሪስ ከ1968 እስከ 1985 ለ18 ዓመታትም የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ አባል፣ ከ1985-1986 ድረስ የመጅሊስ ሊቀመንበር (ፕሬዝዳንት) አማካሪ ሆነው አገለገሉ። በየካቲት 14 ቀን 1987 በአንዋር መስጂድ ግርግርና በመንግስት ጥቃት 10 ሙስሊሞች በመንግስት የጸጥታ አካላት ከተገደሉ በኋላ ሕዝቡን እንዲያረጋጉና የኢድ ሰላት አስተባባሪ ኮሚቴ አባል እንዲሆኑ ተደረገ።

በ1988 ከቢሾፍቱ ከተማ መንግስት ለርሱ ቅርብ የሆኑ ሰዎችን ሰብስቦ የመጅሊስ አመራር ሲመርጥ ሐጅ ዑመር እድሪስም በድጋሚ የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤና የዑለማ ምክር ቤት አባል ሆነው ተመረጡ። እስከ 1992 ድረስም በዚያው ቆዩ።

ከ1993 እስከ ሚያዚያ 2001 የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝዳንት፣ ከሚያዚያ 2001 እስከ መስከረም 2005 የፌደራል መጅሊስ መስጊድና አውቃፍ ዘርፍ ኃላፊ፣ ከ2005 እስከ 2010 የፌደራል መጅሊስ የጠቅላላ ጉባኤው አባል፣ የመስጊድና አውቃፍ ዘርፍ ኃላፊ፣ እንዲሁም የዑለማ ምክር ቤት አባል ሆነው ቆዩ።

ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን ሲመጡ ህዝበ ሙስሊሙና የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴው በመጅሊስ ጉዳይ ጥያቄ ሲያቀርብ መጀሊስን በመወከል ከጠቅላይ ሚ/ሩ ጋር ከቀረቡት መካከል ነበሩ። ከ2010 ሰኔ 26 እስከ ሚያዚያ 23 2011 ድረስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ባቋቋሙት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰብሳቢ ተደርገው ተሾሙ።

በሚያዚያ 23/2011 የጊዜያዊ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ተደርገው ለ6 ወራት ተሹመው በሕገ ወጥ መንገድ ከ3 ዓመታት በላይ ቆዩ። ከሰሞኑ ደግሞ የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ ሐጅ ዑመር እድሪስንና ምክትላቸውን ዶ/ር ጄይላንን ጨምሮ አራት ዑለሞችን ከአመራርነት አንስቶ ወደ ፈትዋ ዘርፍ መደባቸው።

ተቋሙ ከተመሠረተ ጀምሮ ላለፉት 46 ዓመታት በተለያዩ ኃላፊነቶች በአመራር ወንበር ላይ የነበሩት ግለሰብ ተቋሙ በዚህ ሁሉ ዘመኑ ለሕዝበ ሙስሊሙ ተገቢውን አገልግሎት ባለመስጠቱ ይቅርታ ጠይቀው በራሳቸው ፈቃድ ሊሰናበቱ ይገባቸው ነበር። ዕድሜያቸው 90 ሞልቷል። በፈትዋ ክፍል በሙፍቲነት እንዲያገለግሉ ሲወሰን በእምቢተኝነት ሕዝበ ሙስሊሙን ወደ መክፈል ድረስ የሚያደርሰው የስልጣን ፍቅር እንዴት ስር ቢሰድ ነው አቅል እስከ ማሳት የሚያደርሰው?

ከ3 ሳምንታት በፊት የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የመንግስታዊ ተቋማት ሪፎርምን እንዲገበኙ ተሰናድቶ በነበረው ጉብኝት ማጠናቀቂያ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመሩት ስብሰባ ላይ 120 የምንሆን ሙስሊሞች ተገኝተን ነበር። ስለመጅሊስ ምርጫ አጀንዳ ሲነሳ ግን በተለያዩ መድረኮች «አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም» ያሉትን ንግግር ተቃርነው ዛቻ ጀመሩ። ያው በተለመደው የሱፊያ ካባ ስር ሆነው «ደም ይፈሳታል እንጂ አልለቅም» ሲሉ በግልጽ ተናገሩ። ኢናሊላሂ ወኢናኢለይሂ ራጂኡን!
1.6K viewsᴇᴅƦɪS ɴᴀᴡҒᴀʟ, 16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 16:48:48 በዛሬው እለት የሚከተሉት የመጅሊሱ ምርጫ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ተሹመዋል:-

1) ዶ/ር ናስር ዲኖ
2) ዶ/ር ሐሰን ካዎ
3) ዶ/ር አሕመድ ሙስጠፋ
4) አቶ ዐብዱ-ል-ዋሲዕ ዩሱፍ
5) ረዳት ፕ/ር አደም ካሚል
6) አቶ ባህረዲን አወል
7) ሸይኽ ኢልያስ አወል
8) አቶ ዐብዱ-ል-ቃድር ማህ
9)አቶ አደም ቢዳሩ

ተጠባባቂ ተመራጮች ፦

1) አቶ ተሾመ ብርሃኑ ከማል
3) አቶ ዐብዱ-ል-ዐዚዝ ሐሰን
4) አቶ ቢያ ሐጂ
5) ፕ/ር አሕመድ ዘከርያ
6) አቶ አባቢያ አባጆቢር
7) አቶ ዑመር ዐብዱ-ር'ረሕማን
1.5K viewsᴇᴅƦɪS ɴᴀᴡҒᴀʟ, 13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 16:48:48 ዛሬ የተሾሙት ጊዜያዊ የመጅሊስ ስራ አስፈጻሚ አባላት:-

1. ሸኽ ሃጂ ኢብራሂም (ኦሮሚያ)
2. ሸኸ አብዱልከሪም በድረዲን (ደቡብ)
3. ሸኽ አልመርዲ አብዱላሂ (ቤኒሻንጉል)
4. ዶ/ር ጀይላን ገለታ (ኦሮሚያ)
5. ሸኽ ሰኢድ አህመድ ሙስጠፋ (አዲስ አበባ)
6. ሸኽ አብዱልአዚዝ (ሶማሌ)
7. ሸኽ ኑረዲን ደሊል (ምሁር)
8. ሸኽ መሃመድ አህመድ ያሲን (አፋር)
9. ሸኽ መሃመድ ሲራጅ (አዲስ አበባ)
10. ሸኽ አሕመድ አወሎ (አማራ)
11 ሸኽ አህመድ መሃመድ አሊ(ሶማሌ)
12. ዶ/ር ጀማል መሃመድ (ምሁር)
13. ሸኽ አሚን ኢብሮ (ድሬዳዋ)
14. ሸኽ መሃመድ አሚን ሰይድ ዐያሽ (ሃረሪ)
15. ኢንጂ አንዋር ሙስጠፋ (ምሁር)

በተጨማሪም ከታች የተዘረዘሩት ዑለሞች ከአመራር ሀላፊነታቸው ተነስተው ወደፈትዋ ምክር ቤት የተካተቱ የሚከተሉት ናቸው :-
1_ ሙፍቲ ዑመር ኢድሪስ
2_ ዶ/ር ጀይላን ኸድር
3_ ሸኽ ሙሐመድ ሐሚዲን
4_ ሸኽ መኑልከሪም ረሺድ።
1.4K viewsᴇᴅƦɪS ɴᴀᴡҒᴀʟ, 13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 16:48:48 5· የሃገር ሰላም ታውኮ በቆየባቸው ያለፉት በርካታ ወራት ሃይማኖትንና ብሄርን ተገን በማድረግ የእርስ በርስ ግጭት ለመለኮስ አያሌ ትንኮሳዎች አካሄዱ ከርሟል። በቅርቡ በጎንደር ከተማ ውስጥ የተደረገው ሙስሊሞች ላይ የተደረገው የዚሁ ጥቃት ማሳያ ሲሆን መሰል የሽብር ድርጊቶች በየትኛውም አካባቢ ይሁን ወገን እንዳይከሰቱ የበኩላችንን ጥረት እንደምንወጣ እያሳወቅን በተለይም የክልሉ መንግስት ይህንን ተደጋጋሚ ክስተት ለማረም ተጨባጭ እርምጃ እንዲወስድ በዚሁ አጋጣሚ እንጠይቃለን።
6· በመጨረሻም የተቋማዊ ለውጡን ለማሳካት ላለፉት አመታት በተለይም ህጋዊ ጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ እንዳይሰናከል እልህ አስጨራሽ ትግል ስታደርጉ ለከረማችሁ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የመንግስት አካላት ጨምሮ የክልል መጅሊስ አመራር ምስጋናችንን እናቀርባለን።
በተረፈ ህዝበ ሙስሊሙ የኢስላም ፀሀይ በሀገራችን ኢትዮጵያ ከፈነጠቀችበት ጊዜ ጀምሮ አንድነቱ የተጠበቀ መሆኑ ይታወቃል። በዚሁ መሰረት አንድነቱን ማስጠበቅም የሁሉም ሙስሊም ሀላፊነት መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን። እንደ ህዝበ ሙስሊሙ ወኪልነታችን ህዝበ ሙስሊሙ የሚያመልከው ጌታ አንድ፣ ነብያችን አንድ፣ ቂብላችን አንድ፣ ዲናችን ኢስላም እኛም ሙስሊሞች ነን። በመሆኑም በኢስላም ጥላ ስር አንድ ነን። በሌላ ከፋፋይ ስም አንጠራም። መጅሊሱም የሁሉም ሙስሊሞች ተቋም መሆኑን እናረጋግጣለን።

ግንቦት 18/2014
ሸዋል 25/1443
አላሁ አክበር!

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠ/ም/ቤት የጠቅላላ ጉባኤ
1.3K viewsᴇᴅƦɪS ɴᴀᴡҒᴀʟ, 13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 16:48:48 የመጅሊስ ሙሉ መግለጫ
====================

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
በጠቅላላ ጉባኤ አባላት የተሰጠ መግለጫ
ግንቦት 18/2014


ከዛሬ 3 አመት በፊት በዚሁ መድረክ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በደስታ ሲቃ እንባ የተራጩበትና ለተቋማዊ ግንባታ በአንድነት ትልቅ ተስፋ ሰንቀው ያከበሩት ታሪካዊ ክስተት ነበር። ይኸውም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን በጊዜያዊነት ለመምራት በሚያዚያ 23/2011 በሸራተን ጉባኤ በአዲስ መልክ የተቋቋመው 26 ዑለሞችን እና 7 የስራ አመራር ቦርድን ያቀፈ አደረጃጀት መሆኑ ይታወቃል።
ይህ የሸራተን ጉባኤ ለጊዚያዊ መጅሊሱ ያሸከመው አማና:-
• የመጅሊሱን መተዳደሪያ ደንብ፣ የዑለሞች የአንድነትና የትብብር ሰነዶችን ለባለ ድርሻ አካላት በማቅረብ ማፅደቅ፤
• የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በአዋጅ የተረጋገጠ ህጋዊ እውቅና እንዲያገኝ ክትትል ማድረግ፤
• ምርጫ በማድረግ ተቋሙን የሚመሩ የህዝበ ሙስሊሙን ተመረጮች በማስመረጥ ተቋሙን ለተመራጮች ማስረከብ መሆኑ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ ከአዋጁ በስተቀር የስራ አስፈፃሚው አንዱንም ተግባራዊ ማድረግ ሳይችል ሶስት አመታትን አስቆጥሯል።
ጉባኤው በጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካኝነት በተቋቋመው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ኮሚቴ (በ9ኙ ኮሚቴ) የተጠራና ጠቅላይ ሚኒስትሩ የከፈቱትን፣ የሰላም ሙኒስትር ሚኒስትርም በታዛቢነት የታደሙበት እና ከተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የተወከሉ ከ500 በላይ የሚሆኑ ዑለሞች፣ምሁራን፣ዱአቶች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙበት ታላቅ ሀገራዊ ሸንጎ ነበር።የዚህ ሸንጎ ውጤት የሆኑት 26 ዑለሞች እና 7 የስራ አመራር ቦርድ አባላት ለጉባኤው ተሳታፊዎች መጅሊሱን በጊዚያዊነት እንዲመሩ በጋራ ኮሚቴው የተመረጡ መሆናቸው ተነግሮና በጉባኤ ፊት እንዲቀርቡ ከሆነ በኃላ በሙሉ ድምፅ (በኢጅማእ) የተመረጡ ነበሩ።
ውሳኔውም በህዝበ ሙስሊሙ ዘንድ ከፍተኛ ደስታን የፈጠረ ከመሆኑም ባሻገር ተቋሙም ለውጡ መስመር ይዟል የሚል ከፍተኛ ተስፋ እንዲሰንቅ አድርጎት ነበር።
ሆኖም ጊዚያዊ ስራ አስፈፃሚው አመራር የተሰጠውን ኃላፊነት መወጣት ሳይችል ይባስ ብሎ
– የሸራተኑን ጉባኤ ውሳኔ በመጣስ
– በዱባይ የተደረገውን ስምምነት በመጣስ
– የሹራ (የውይይት) አደብን በመጣስ
– የክልል መጅሊሶችን እንዳይደራጁ በግራ ስምምነት የተደራጁትንም እንዲፈርሱ የአስተዳደር ስርአት በመጣስ ጣልቃ መግባት
-ከሁሉም በላይ የህዝበ ሙስሊሙን አንድነት ከፍተኛ አደጋ ላይ በመጣል---
በማን አለብኝነት ስሜት በጉባኤው የተሾሙትን በርካታ ዑለሞች እና የስራ አመራር ቦርዱን ህገ ወጥ በሆነ መልኩ በማገድና በማባረር ተቋሙ የጥቂት ግለሰቦች መፈንጫ እንዲሆን አድርገውታል። በዚህም ድርጊታቸው ህዝበ ሙስሊሙ ሀገራዊ ሚናውን በተገቢው መልኩ እንዳይወጣ አድርገዋል።
ጊዚያዊው የስራ አስፈፃሚው የህዝብ አማናን ካለመወጣቱ ባሻገር በርካታ ህገ-ወጥ ተግባራትን ሲፈፅም በመቆየቱ በህገ-ወጥ መልኩ የተባረሩ ዑለሞች እና የስራ አመመራር ቦርዱ እንዲሁም ህዝበ ሙስሊሙ ሲታገላቸው ቆይቷል።እየታገላቸውም ይገኛል።
ከዚህ ሁሉ አፍራሽ ተግባራቸው ጀርባ መንግስት እንዳለና ማንም የሚነቀንቀን የለም በሚል የሚያስተላልፋት መልእክት በመንግስትና በህዝበ ሙስሊሙ መካከልም ከፍተኛ የሆነ ቅሬታ እንዲፈጠር ምክንያት ሆነዋል።
የዑለማዕ ም/ቤቱ የሀገራችንን ተጨባጭ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ነገሮችን በስክነት እና በከፍተኛ ትእግስት ሲከታተል ቆይቷል። በመጨረሻም 25 ዑለማዎች ከ መጋቢት 17 እስከ 24/2014 በመተዳደሪያ ደንቡ ዙሪያ የመንግስት ታዛቢዎች ባሉበት ጥልቅ ውይይት ተደርጎበታል። ከውይይቱ በኃላም ለህዝበ ሙስሊሙም በመንግስት ሚዲያ ሸዋል 10 ከተለያዩ አካላት 105 ዑለሞች፣ ሙህራንና ዳዒዎችን በማሳተፍ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ተጨማሪ ረቂቅ ሰነዱን የሚያዳብሩ አስተያየቶች ከተሰበሰቡ በኃላ በ25 በሸራቶን በተመረጡ ዑለሞች እንደሚፀድቅ በሙሉ ድምፅ ስምምነት ላይ የተደረሰ መሆኑን በፊርማቸው ጭምር አረጋግጠዋል።
በዚሁ መሰረት የዑለማእ ም/ቤቱ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ጥልቅ ውይይት ከተደረገና ተገቢ የሆኑ ማሻሻያዎች ከተካተቱበት በኃላ ውይይቱ ላይ የተገኘን የዑለማዕ ም/ቤት አባላት መተዳደሪያ ደንቡን በሙሉ ድምፅ አፅድቀነዋል። ሆኖም ለውጡ እውን እንዲሆን ያልፈለጉና ቃላቸውን ያጠፋ ጥቂት የዑለማዕ ም/ቤት አባላት ከውይይቱ ወደ ኃላ ያሉ መሆናቸውን ለህዝበ ሙስሊሙ ማሳወቅ እንወዳለን።
በመሆኑም ብዝኋኑ የጠቅላላ ጉባኤው አባላት ስብሰባዎችን በመቀጠል
1. የመተዳደሪያ ደንቡን አፅድቋል።
2. የምርጫ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስይሟል።
3. የምርጫ መረሃ ግብር ተቀምጧል።
4. አላግባብ ታግደው የነበሩት የዑለማ እና ስር አመራር ቦርድ አባላት ወደ ስራቸው እንዲመለሱ ተወሰኗል።
5. በሙስሊሙ አንድነት እና ተቋማዊ ሂደት ላይ ከፍተኛ እንቅፋት የነበሩትን አመራር በመቀየር ካሉት የጠቅላላ ጉባኤ አባላት መካከል አዳዲስ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላትን ሰይሟል። እንዲሁም የሙስሊሙን መንፈሳዊና ሐይማኖታዊ ጉዳዮች የሚመራ ራሱን የቻለ አካል ተቋቁሟል።
እነዚህን ዋና ዋና ውሳኔዎች መሰረት በማድረግ ከአራት ወራት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ሁሉን አቀፍ ህዝባዊ መጅሊስ ለማቋቋም የሚደረገውን ሂደት ተጨባጭ ማሳያዎች እንደሚሆኑ ከፍተኛ እምነት አለን።
በመሆኑም ይህንን ሂደት እስካሁን ድረስ ከ3 አመታት በላይ ሳይሳካ በመዘግየቱ ህዝበ ሙስሊሙን ይቅርታ እየጠየቅን አሁን በተፈጠረው ዳግማዊ ዕድል በመጠቀም ማሳካት ይቻል ዘንድ ይህ ባለ 6 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተናል።
1· የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ጠቅላላ ጉባኤ የተቋሙ የበላይ አካል እንደመሆኑ መጠን መተዳደሪያ ደንብ በተሰጠው ስልጣን የወሰናቸውን ውሳኔዎች በመተግበር መንግስት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አበክረን እንጠይቃለን
2. የሙስሊሙን አንድነት የማይሹ ከመጅሊሱ አመራር ድረስ በተቆናጠጡት ስልጣን እና በጣት የሚቆጠሩ ግለሰቦች ለሃገር ሰላም እና አንድነት ሲባል ለአመታት በትዕግስት እና በመቀራረብ ሲደረግ የነበረው ጥረት ካሁን በኋላ ሙስሊሙ እንደማይታገሳቸውና ከድርጊታቸው የማይታቀቡ ከሆነ ለህግ እንደሚያቀርባቸው አጥብቀን እናስገነዝባለን፣
3. የተቋም ግንባታ ሂደት አላማውን ለማሳካት በቆረጡ አካላት ካልተመራ ትርፉ ከፍተኛ የሃገር ሃብት ብክነት ብቻ ሳይሆን የተቋም ብሎም የህዘብና የሃገር ሰላም እስከማወክ እንደሚደርስ የመጅሊሳችን ያለፉት 3 አመታት ጉዞ አሳይተውናል። በመሆኑም ይህ ዳግም እንዳይከሰት ህዝበ ሙስሊሙ፣ የክልል መጅሊስ ተወካዮች እና የሚመለከታችሁ አካላት ይህንን ሽግግር በማሳካት ረገድ የበኩላችሁን ሚና እንድትጫወቱ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን።
4. በፀደቀው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት የምርጫ አስፈፃሚ ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን እስከ መስከረም 30 ምርጫው እንዲደረግ የወጣውን መርኃ ግብር ለማሳካት ህዝበ ሙስሊሙ በንቃት እንዲከታተል እና እንዲሳተፍ ጥሪ እናቀርባለን።
1.4K viewsᴇᴅƦɪS ɴᴀᴡҒᴀʟ, 13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 21:51:02 ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ረሂመሁላህ

قال الإمام شيخ الإسلام ابن تيمية
"الحق كالذهب الخالص كلما امتحن ازداد جودة والباطل كالمغشوش المضيء إذا امتحن ظهر فساده” [الجواب الصحيح 88/1]

« ሐቅ እንደተነጠረ ንፁህ ወርቅ ነው ፤ በተፈተነ ቁጥር ጥራቱ ይጨምራል። ባጢል ደግሞ እንደ አርቲፊሻል ወርቅ ነው ፤ በተፈተነ ቁጥር ግድፈቱ ይጎላል!! » [አልጀዋቡሰሂህ 1/88]

https://t.me/edriszulbijadeyn
1.2K viewsᴇᴅƦɪS ɴᴀᴡҒᴀʟ, 18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 05:52:16 أغلب النّاس الذين تسمع عليهم كلاماً سيّئًا خلف ظهورهم ،
عند معاشرتهم ، تجدهم أروع وأنظف من المنافق الذي تكلّم عنهم

الصباح الخير


https://t.me/edriszulbijadeyn
1.4K viewsᴇᴅƦɪS ɴᴀᴡҒᴀʟ, 02:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ