Get Mystery Box with random crypto!

የመንግሥት ማስጠንቀቂያ ~'በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የሚሠሩ አካላት ከድ | የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command

የመንግሥት ማስጠንቀቂያ

~"በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የሚሠሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል "-ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

"በኢትዮጵያ እና በሱዳን ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የሚሠሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል " ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አሳሰቡ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ጉዳዩን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ እና የሱዳን ሕዝቦች ብዙ ፈተናዎችን እየተጋፈጡ በሚገኙበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፤ የሐሰት ውንጀላዎችን በማሰራጨት የፖለቲካ ዓላማቸውን ለማሳካት የሚጥሩ ወገኖች እንዳሉ ጠቁመዋል።

እነዚህ አካላት "ኢትዮጵያ በሱዳን ድንበር አካባቢ ወታደሮቿን አስጠግታለች" የሚል የሐሰት መረጃ እያሰራጩ መሆኑንም ነው ያነሱት፡፡

ይህን የወንድማማች ሀገራትን ግንኙነት የሚያሻክር የሐሰት ውንጀላም ኢትዮጵያ በጽኑ እንደምታወግዘው አስገንዝበዋል፡፡

በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ያለው ጉዳይም በውይይት እንደሚፈታ እምነታቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

https://t.me/CommandoAndAirborneCommand

YouTube