Get Mystery Box with random crypto!

ክርስቲያናዊ ወጣት

የቴሌግራም ቻናል አርማ cherstianawiwetat — ክርስቲያናዊ ወጣት
የቴሌግራም ቻናል አርማ cherstianawiwetat — ክርስቲያናዊ ወጣት
የሰርጥ አድራሻ: @cherstianawiwetat
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.98K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል እኛ ወጣቶች እንዴት መንፈሳዊነትንና ዘመናዊነትን አጣምረን መሄድ እንችላለን? የሚለውን ሀሳብ እንማማራለን። ጆይን በማለት ሥርዓትን እንወቅ እናሳውቅ።
@wetatZeTewahido

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-12-20 23:33:50 https://t.me/orthodoxAPOLOGETICS/565
4.6K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, 20:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-15 07:41:20
+++በዓለም እጅግ ውዱን ነገር አምጡልኝ!+++

በቀደመው ዘመን የሚነገር አንድ አፈ ታሪክ እንዲህ ይላል:

እግዚአብሔር ለቅዱሳን መላእክቱ "ወደ ምድር ሄዳችሁ እጅግ ውድ የሆነውን ነገር አምጡልኝ" አላቸው።

በዚህም መሠረት አንዱ መልአክ ፤ ሌላውን ሰው ለማዳን ብሎ ራሱን አሳልፎ የሰጠን ሰው "የደም ጠብታ" ይዞ ወደ እግዚአብሔር ቀረበ ፤ እግዚአብሔርም ተመልክቶ "የከበርከው መልአክ ሆይ! እውነት ነው! በእኔ ዘንድ ይህ ደም ውድ እና የከበረ ነው ፤ ነገር ግን ይኼ በዓለም ካሉት ሁሉ እጅግ ውዱ እና የከበረ ነገር አይደለም" አለው።

ሌላ መልአክ ደግሞ ፤ የታመሙትን ለማዳን ሕክምና ስትሰጥ በአሰቃቂ ሕመም ተይዛ የሞተችን ነርስ "የመጨረሻ እስትንፋስ" ይዞ ወደ እግዚአብሔር ቀረበ ፤ እግዚአብሔርም ተመልክቶ ፈገግ ብሎ "የከበርከው መልአክ ሆይ! እውነት ነው! በእኔ ዘንድ ስለ ሌሎች ራስን አሳልፎ መሥጠት በጣም ውድ እና የከበረ ነው ፤ ነገር ግን ይኼ በዓለም ካሉት ሁሉ እጅግ ውዱ እና የከበረ ነገር አይደለም" አለው።

በመጨረሻም አንድ መልአክ ፤ ንስሓ ገብቶ ወደ እግዚአብሔር የተመለሰ "የአንድ ኃጢአተኛን ዕንባ" በትንሽ ብልቃጥ ይዞ ወደ እግዚአብሔር ቀረበ ፤ እግዚአብሔርም ፊቱ በደስታ በርቶ እንዲህ አለ "የከበርከው መልአክ ሆይ! እውነት ነው! በዓለም እጅግ ውድ የሆነውን ነገር ይዘህልኝ መጥተኻል ፤ የመንግሥተ ሰማያትን በር የሚከፍተው የንስሓ ዕንባ!"

Source and Image Credit: John Henry Harkonen [From Philokalia]

@Slehiwetwe ይቀላቀሉን።
4.4K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, 04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-14 07:54:27
ሰላም ለናንተ ይሁን ወንድምና እህቶቼ ይህ የምትመለከቱት ወድማችን የ17 አመታ ታዳጊ ሲሆን በአሁን ሰአት ባገጠመው የኩላሊት ህመም ምክንያት ሁለቱም ኩላሊት መቀየር ስላለባቸው ህክምና ላይ ይገኛል ሆኖም ህክምናውን ለመከተታል የሚያስፈልገው ወጪ ከአቅም በላይ ስለሆነበት በቻልነው ልክ ሁላችንም ብንተባበረው።
ያለንን እየሰጠን፣ ምንም ባይኖረን ደግሞ ቢያንስ ቢያንስ እየጸለይን እና ለሌሎች ሼር እያደረገን ብንረዳው፤ ወንድማችን ይድንልን ይሆናል። እባካችሁ ይሄን እያያችሁ አትለፉ
CBE ACC
1000357655327
1000139423244

ለበለጠ መረጃ፡ 0929133563
3.5K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, edited  04:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-13 07:26:48
#ክርስቲያን_ነህ...

|" ክርስቲያን ነን ብለን ራሳችንን ለመጥራት ከደፈርን፣ ከክርስትናችን መከራን ብቻ እንጠብቅ፤ ክርስቶስ ይህቺን ምድር ከረገጠበት ጊዜ አንስቶ ክርስትና መከራን መቀበልና መስቀልን መሸከም መገለጫው ሆኗል። የርሱን ሕይወት በመከተል በየዕለቱ በምሥጢራዊውና ለየግላችን በተሰጠን መስቀል በጭንቅም ቢሆን በመንፈስ ልንለወጥ ይገባናል፤ ለመንፈሳዊ እርገት ትክክለኛውና ብቸኛው መንገድ #መስቀሉ ነውና! ከክርስቶስ ጋር በሕይወት ለመነሣት፣ በመጀመሪያ ልክ እንደርሱ በትህትና ዝቅ ልንል ይገባናል። የክርስቶስን ሰማያዊ መንግስት የዚህ ዓለም ተጠሪ ለጥቂት ቅጽበታት እንኳን የመቋቋም አቅም የለውም፤ ስለዚህ በዚህ ብርሃንን በሚገፋ ዓለም ውስጥ በእውነት ክርስቲያን መሆንና እንደክርስቲያን በተግባር መኖር ከባድ ብቻ ሳይሆን የማይቻል እስኪመስለን ደርሷል። በይበልጥ በእውነት በተኖረና በተተገበረ መጠን፣ የድሮውን ማንነት በጭንቅና በትግል የሚያጠፋውን መስቀላዊ ሕይወት ማንም ሰው እያወቀ ሊገባበት አይፈቅድም፤ መስቀሉን ተሸክሞ ክርስቶስን መከተል ይዞት የሚመጣውን መከራ መቀበልን አይመርጥም። ስለዚህም ሁሌም ሕይወታችንን በተለያዩ ማታለያዎች እያጠርን ይህን የውሸት ክብርን እያጠፋ ትህትናና ፍቅርን የሚገነባን የክርስትና መንገድ፣ እንደአመጽ ፊታችንን እያዞርን በግማሽ ክርስቲያኖች ለመሆንና ከሁለቱም ዓለም የፈለግነውን እየመረጥን በምቾት ያለምንም መከራ ለመኖር ሁሌም እንጥራለን። ነገር ግን መምረጥ ይገባናል፤ መኖር የምንችለው ወይ እንደዚህ ወይም እንደሌላኛው ዓለም ሰው ነው። የሁለት ዓለም ሰዎች መሆን ግን #በክርስትና_ውስጥ_የሌለና_ያልተሰጠ_አማራጭ_ነው።"|

+.#አባ_ሴራፊም_ሮዝ
2.8K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, 04:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-12 16:09:48 ""#በዓታ_ለማርያም
#እውነተኛዋ_ታቦት_እመቤታችን
#ባለበት_ቤተመቅደስ_ገባች

#በዲያቆን_ጥበቡ_ማሞ

#አዳምጡ_መልካም_ቆይታ

@yekidusantarikachewhiywetachew
2.1K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, 13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-12 15:31:18 እቺ ናት የኔ ሴት

የሴትነት ልኬት ምንድነው?
ሁላችሁም እህቶች አድምጡት።

በወንድም አቡ

@ApostolicSuccession
2.2K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, edited  12:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-12 15:22:39
"ለወፎች ክንፍ የተሰጣቸው"

ለወፎች ክንፍ የተሰጣቸው በወጥመድ እንዳይያዙ ነው። ሰዎችም የማሰቡ ኃይልን የተሰጣቸው ኃጢአትን እንዲያስወግዱ ነው። እንግዲህ እንዲህ የማሰብ ኃይል ተሰጥቶን ሳለ ይባስ ብለን ከምድር አራዊት በታች የማናስተውል ከኾንን ሊደረግልን የሚችል ምህረት ወይም ይቅርታ እንደምን ያለ ምሕረት እንደምንስ ያለ ይቅርታ ነው?

በወጥመድ ተይዛ የነበረች ወፍ ድንገት ከወጥመዱ ብታመልጥ፤ ወደ ወጥመድ ገብቶ የነበረ አጋዘን ወጥመዱን በጣጥሶ ቢሄድ ከእንግዲህ ወዲህ በተመሳሳይ ወጥመድ እነዚህን መያዝ ከባድ ነው። የሕይወት ተሞክሮ ለሁለቱም ጥንቃቄን አስተምሯቸዋልና። እኛ ግን ምንም እንኳ በተመሳሳይ ወጥመድ ብንያዝም ተመልሰን ወደዚያ ወጥመድ እንወድቃለን፣ ምንም እንኳን በለባዊነት የከበርን ብንኾንም አእምሮ እንደሌላቸው እንሰሳት እንኳን ቀድመን አናስብም፤ አንጠነቀቅም!

ሴትን በማየት እልፍ ጉዳቶችን ተቀብለን ወደ ቤታችን የተመለስነው፤ በዝሙት ተመኝተንም ስናበቃ ለአያሌ ቀናት ያዘንነው ስንቴ ነው? ነገር ግን ከዚያ በኋላም ቢሆን በዚሁ ጉዳይ ላይ ጠንቃቆች አልኾንም፤ አንዱን ቁስል ሳናገግም ወደዚያ ክፉ ጠባይ እንወድቃለን፣ በተመሳሳይ መንገድ እንያዛለን፤ እጅግ ጥቂት ለኾነች የደስታ ሽርፍራፊ ብለንም ረጅምና ተደጋጋሚ ሥቃይን እንቀበላለን።

ዘውትር "በወጥመዶች መካከል እንደምትኼድ በገደልም መካከል እንደምትመላለስ ዕወቅ" የሚለውን ኃይለ ቃል ደጋግመን ለራሳችን ብንነግረው ግን ከእነዚህ ጉዳቶች ኹሉ እንጠበቃለን (ሲራ 9:13)

~ በእንተ ሐውልታት
2.1K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, 12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-10 12:39:42
1.9K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, 09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-09 08:52:05 ጴጥሮስን ለታላቅ ንስሓ የቀሰቀሰው የዶሮ ጩኸት ነበር ... ‹የዶሮ ጩኸት ጴጥሮስን ለንስሓ አበቃው› የሚለው ታሪክ ከዶሮ ጩኸት አልፎ እልፍ ሰባኪያን ‹ንስሓ ግቡ› እያሉ ሲጮኹ እየሰማን ምንም ለማይመስለን ለእኛ ለልበ ደንዳኖቹ መልእክቱ ምን ይሆን? የዶሮዎቹን ጩኸት ሰምቶ በመመለስ ፈንታ የዶሮዎቹን የአጯጯህ ስልት እያወዳደርን ሰባኪያን ለምናማርጥ ለእኛ መልእክቱ በእርግጥ ምን ይሆን?

በእርግጥ የዶሮውም እድል የሚያስቀና ነው፡፡ አንድ ጊዜ ጮኾ የወደቀውን ጴጥሮስ እንዲነሣ መቀስቀስ መቻሉ የታደለ ሰባኪ ያደርገዋል፡፡ ብዙ ጊዜ ስንጮኽ ውለን አንድ ሰው ለንስሓ ማብቃት ላልቻልን ሰባኪያን ይህ ዶሮ ምንኛ የሚያስቀና ነው? ለነገሩ በልማዱ ዶሮ ጮኾ ሌሎቹን ከማስነሣቱ በፊት እሱ ተነሥቶ ክንፉን እያርገበገበ ከፍ ከፍ ይላል፡፡ እኛ ግን ራሳችን በኃጢአት ተኝተን ሌላውን ለንስሓ ለመቀስቀስ የምንሞክር እንቅልፋም ዶሮዎች ስለሆንን በጩኸታችን የረበሽነው እንጂ የቀሰቀስነው ሰው የለም፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
2.5K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, 05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-06 15:38:33 "ወዳጄ ሆይ ሮማውያን ወታደሮች ጎንጉነው በጌታችን እራስ ላይ እሾህ እዳቀዳጁት ባሰብህ ጊዜ እጅግ ማዘንህ አይቀርም ። ሆኖም አንተም እሾህ የተባለውን አንድ ኃጢአት በሰራህ ቁጥር በጌታችን ላይ የተደፉትን እሾኾች ቁጥር እንደጨመርህ አስብ ።በፈጣሪ የማያምኑት ሮማውያን ወታደሮች ከጎነጎኑት እሾኽ በላይ የጌታችንን እራስ የበለጠ ዘልቆ የሚወጋው ደሙን አፍስሶ ያዳነን እኛ ክርስቲያኖች በኃጢአታችን የምንጎነጉነው የእሾኽ አክሊል ነው ።{ስለመተላለፋችን የቆሰለው አምላክ በመተላለፋችንም ይቆስላል ።!}

{በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ከሚለው ርዕስ የተወሰደ )

[ ሕማማት]
{በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ}
:
መድኃኔዓለም ሆይ አባት ሆይ ይቅር በላቸው በማለት በታላቅ ቃል በመስቀል ላይ ፥ ለተናገረ ቃልህ ሰላም እላለሁ በመስቀል ላይም በሰቀሉህ ጊዜና ጎንህን በጦር በወጉ ጊዜ አንዳችም የተቃውሞ ትንፋሽ ላልተነፈሰ እስትንፋስህም ሰላም እላለሁ ።
መድኃኔዓለም ሆይ ጻድቃንን ያይደለ ኃጥአንን ለማዳን በራሱ ደም ራሱ ለተጥለቀለቀ ስነ መልክህ ሰላም እላለሁ !
( መልክአ - መድኃኔአለም )27
2.0K viewsΠαρακαλώ συγχωρήστε μας, 12:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ