Get Mystery Box with random crypto!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ በበ | ቦሌ ኮሚዩኒኬሽን/Bole Communication

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ በበኩላቸው እንደአገርና እንደከተማ ባለፉት አራት ዓመታት በርካታ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን አውስተው፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያሉ መንገዶች ውብና አረንጓዴ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች የተለያዩ አካላት ተሳታፊ መሆናቸውን ተናግረዋል። “በልማት ሥራችን ተሳታፊ የሆኑ በጎ አልሚ ባለሀብቶችን በማስተባበርና ለሥራቸው ዕውቅና በመስጠት የከተማችንን ውበት ለማስጠበቅ እየሠራን ነው” ያሉት ወ/ሮ ይመኙሻል፣ የቦሌ ክፍለ ከተማ በአዲስ አበባ ከተማ በሚከናወነው የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ሥራ ከቀዳሚዎቹ መሀል እንደሚገኝ በመግለጽ ለዚህ ውጤት መገኘት የክፍለ ከተማው አስተዳደር፣ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤትና ባለድርሻ አካላት ላደረጉት አስተዋጽኦ እንዲሁም የንኮማድ ኮንስትራክሽን ላሳየው አጋርነት በከተማው አስተዳደርና በቢሮው ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የየንኮማድ ኮንስትራክሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ የምሩ ነጋ ድርጅታቸው መንግሥት የቀየሰውን የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ ለማገዝ በሚገኝበት አካባቢ የመንገድ አካፋይ የአረንጓዴ ልማት ሥራን ለማከናወን መነሳሳቱን ገልጸው፣ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውን ሥፍራ ለማልማት ከክፍለ ከተማው አስተዳደር ጋር በመነጋገር እስከ መስከረም ወር 2015 ድረስ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አክለው ተናግረዋል። “አገራችን የጋራችን በመሆኗ ለአገራችን ልማት ኃላፊነቱ የራሳችን መሆኑን ተረድተን አቅም ያለን ባለሀብቶች ለኢትዮጵያ ብልጽግናና ለማኅበረሰብ ልማት ድርሻችንን ልንወጣ ይገባል” ሲሉ አቶ የምሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ግንቦት 6/2014