ራስህን እመነው! ችግር ሲገጥምህ የምትሸሽ ወይኔ አለቀልኝ ብለህ የምትፈራ ከሆነ ችግርህ ሁሌም እንደ ጥላህ ሲያሳድድህ ይኖራል! አለበለዚያ ግን ምናባቱ ያመጣል ብለህ የገጠመህን ችግር ከተጋፈጥከው እንደ ንስር ተረጋግተህ ከላይ ወደታች ካየኸው ያ መከራ እንደ ዝሆን ግዙፍ ቢሆን እንኳን እንደ ቁጫጭ አንሶ ይታይሀል። ወዳጄ ከፈጣሪ ቀጥሎ ራስህን እመነው ካንተ አቅም በላይ የሆነ ምድራዊ ፈተና የለም! ምክንያቱም ለማሸነፍ ነው የተፈጠርከው! @Inspire_Ethiopia 234 views..., 18:53