#Dessie
ደሴ ከተማን ሙሉ በሙሉ ማዳረስ የሚያስችል ከ605 ሺህ ሊትር በላይ ዘይት ከፌቤላ የዘይት ማምረቻ ኢንዱስትሪ ጋር በመተባበር በተያዘው ሳምንት ለነዋሪዎች እንደሚከፋፍል የከተማዋ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
የዘይት አቅርቦቱ በ 'ሸማች ማህበር' በኩል ይቀርባል የተባለ ሲሆን በገበያው ላይ የሚስተዋለውን የዋጋ ንረት ለመከላከል የቁጥጥር ስራም እየተሰራ ነው ተብሏል።
በከተማዋ በሸማች ማህበራት በኩል የሚቀርበው የዘይት ዋጋ ፡-
1. ባለ 3 ሊትር 290 ብር ከ06 ሳንቲም
2. ባለ 5 ሊትር 474 ብር ከ40 ሳንቲም
3. ባለ10 ሊትር 936 ብር ከ69 ሳንቲም
4. ባለ 20 ሊትር 1 ሺህ 834 ብር ከ66 ሳንቲም
5. ባለ 25 ሊትር 2 ሺህ 277 ብር ከ90 ሳንቲም መሆኑ ተገልጿል፡፡
t.me/asosaonline