Get Mystery Box with random crypto!

አርጋኖን ስነ-ግጥም ና ጭውውት ..On.Tg

የቴሌግራም ቻናል አርማ areganone834 — አርጋኖን ስነ-ግጥም ና ጭውውት ..On.Tg
የቴሌግራም ቻናል አርማ areganone834 — አርጋኖን ስነ-ግጥም ና ጭውውት ..On.Tg
የሰርጥ አድራሻ: @areganone834
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 931
የሰርጥ መግለጫ

ባተሌው....ገጣሚ ..
.
ስነ-ግጥሞች እንዲሁም..
.
.ወጎች..ጭውውቶች ይቀርብበታል
በተጨማሪም..መጽሀፍቶችን
እናቀርባለን * ልብ ወለድ
* ፋልስፍና
* ሀይማኖታዊ መጸሀፈቶች ይገኛሉ ይጠይቁ ሀሳብ አስተያየት ካሎት
👇
@yarbegnawlij
@Atsewdua Inbox

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-30 19:04:11 " እናንተ ማንንም ለመሆንና ማንንም የመምሰል ህይወት ለመኖር አልተፈጠራችሁም። እናንተ የተፈጠራችሁት እናንተን ለመሆንና ለመምሰል ብቻ ነው። እራሳችሁን እንደ እከለ ብሆን፣ እንደ እንትና ብሆን፣ እንደ እሱ....እንደ እሷ ሆኘ ብፈጠር ኖሮ እያላችሁ የሰነፍ ሰው ምኞት አትመኙ። እራሳችሁን ሆናችሁ ስለተፈጠራችሁ ደስ ይበላች፤ እንጅ እራሳችሁን ሆናችሁ መፈጠራችሁን በፍፁም አትጥሉ። አምላክ እናንተን እናንተ አደርጎ የፈጠራችሁ በእናንተ የሚሰራው ስራ ስላለው ነውና ሌላውን የመሆንን ህይወት ከመመኘት ወጥታችሁ በእናንተ ልሰራ ያሰበውን #ዓላማ ወደ ማወቅ ህይወት ለመግባት እራሳችሁን ለተ ቀን አዘጋጁ።
267 viewsŻel@lem Ãdineŵ, 16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 10:24:04 የሰው ልጅ ሲያገኘው የሚችለውን ትልቁን ፀጋ ሌሎችን አለመከተል ነው።

ምንጭ ፦ ንቃተ ህሊና ( ኦሾ)
ተርጓሚ ፦ አና ፍራንክ

እኔ «ኑ ተከተሉኝ» ልላችሁ አልችልም። መጀመሪያ ይህንን የተናገሩት የሰው ልጅን ረዳት አልባ አድርገውታል። የሚፈልጉትን ነገር አሟልተውበታል። ሰዎች በራሳቸው ብቻቸውን መሆንን (ለብቻ መቆምን) አይፈልጉም። የራሳቸውን መንገድ የመፍጠር፣ በፈጠሩትም መንገድ
የመጓዝ ወኔ የላቸውም። መመራት ይፈልጋሉ።

የምትመሩ ከሆነ አይኖች እንኳን ቢኖራችሁ ቀስ በቀስ እንደምታጧቸው አታውቁም። በክሪሽና፣ በቡድሀ ወይም በሌላው አያኖች መመልከት ትጀምራላችሁ። የእናንተ አይኖች አስፈላጊነት ያበቃል። እንደውም አይኖቻችሁ ችግር ይፈጥሩባችኋል። አንድ መሪ የሚፈልገው በራሳችሁ አይን መመልከት አቁማችሁ በእሱ አይኖች እንድትመለከቱ ነው፤ የራሳችሁን እግር ትታችሁ በእሱ እግሮች እንድትጓዙ ነው። በራሳችሁ ማመን ትታችሁ በእሱ እንድታምኑ ነው። ይህ ለእኔ ወንጀል ነው። እንደዚያ ካደረግኩ እናንተን አካለ-ጉደሎ፣ ሽባ እያደረግኳችሁና እያጠፋኋችሁ ነው። ይህንንም በመላው አለም ሲደረግ ማስተዋል ትችላላችሁ። መላው የሰው ልጅ በእንደዚህ አይነት ንግግሮችና ይህን በሚናገሩ ሰዎች ጠፍተዋል። እናንተም ለዘላለም መጥፋት ካልፈለጋችሁ በስተቀር እኔን ፈፅሞ ልትከተሉ አይገባም! እኔን ከተከተላችሁ በርግጠኝነት ትጠፋላችሁ፡፡ ስለዚህ እኔ ‹ኑ እና ከእኔ ተጋሩ> እንጂ <ኑ ተከተሉኝ> ልላችሁ አልችልም፡፡ ደግሞስ እኔን የምትከተሉት እኔ ማን ሆኜ ነው?!

እያንዳንዱ ሰው በራሱ ልዩ ፍጡር በመሆኑ አንድን ሰው መከተል ከጀመራችሁ ወዲያውኑ ማስመሰል እንደምትጀምሩ አስተውሉ። የራሳችሁን ማንነት ታጣላችሁ፤ አስመሳይና ግብዝ ትሆናላችሁ፤ ራሳችሁን መሆን ትታችሁ ሌላ ሰውን ትሆናላችሁ፤ ትከፋፈላላችሁ። ሂንዱ፣ አይሁድ፣ ቡዲስት የሚል ጭምብል ይኖራችኋል። ይህም እናንተና ያ የምትከተሉት ሰው የፈጠራችሁት ጭምብል እንጂ የእናንተ እውነተኛ መልክ አይደለም። የምትጓዙት ከማንነታችሁ በተቃራኒ ስለሆነ ትሰቃያላችሁ። መላው የሰው ልጅም ስቃይ ላይ ነው። ምክንያቱም ሁሉም ልጅ ወላጆቹን፣ ጎረቤቶቹን፣ የትምህርት ቤት ጓደኞቹን፣ አስተማሪዎቹን . . . ለመምሰል ይሞክራል። እነሱም ሊያስገድዱት ይሞክራሉ።

እኔ በልጅነቴ የነበረውን ሁኔታ አስታውሳለሁ። የጄይና እምነት ከሚከተል ቤተሰብ መወለዴ ድንገተኛ አጋጣሚ ነበር። አባቴም እንደ ማንኛውም ሰው ወደ ቤተ-መቅደስ ቢወስደኝም፣ እሱን መምሰል እንደሌለብኝ ዘወትር ይነግረኝ ነበር። እሱ የአያት የቅድመ አያቶቹን መንገድ ተከትሎ ያገኘው ነገር አልነበረም። «የእኔን መንገድ እንድትከተል አልፈልግም። እኔ የተከተልኩት መንገድ ይህ ነው ፤ እኔ ስሰግድ የኖርኩት ለእነኚህ አማልክት ነው ፤ እነኚህን ፀሎቶች ስጸልይ ኖሬአለሁ እያልኩ ላሳይህ እችላለሁ። ለእኔ ግን ምንም የፈየደልኝ ነገር የለም። አንተም እንድታደርገው ላስገድድህ አልችልም። በተቃራኒው አንድ ነገር በውል ካልተሰማህ በስተቀር እንዳታደርገው እመክርሀለሁ።››

እኔም በህይወቴ ማንንም አልተከተልኩም። ይህ እጅግ በጣም ከፍተኛ ጠቀሜታ ሰጥቶኛል። የሰው ልጅ ሊያገኘው የሚችለውን ትልቁን ፀጋ አግኝቻለሁ። ይህም ሌሎችን አለመከተል ነው።

ራሴን ሆኜ ለመኖር ሞክሬአለሁ።
ይህንን ለማድረግ ታድያ ድፍረት ያስፈልጋችኋል፤ ጥሩ እውቀት ያሻችኋል፤ እውነትን በራስ መፈለግ መቻልን ይጠይቃችኋል፤ ትክክለኛ የሆነ ፍለጋ ማካሄድ ይኖርባችኋል።

ያኔ ነው አደጋን መጋፈጥ የሚቻለው። አለበለዚያ በዙሪያችሁ ወደ እነሱ ሊወስዷችሁ ያሰፈሰፉ ብዙዎች አሉ።

የትኛውም ቡዲዝምም ሆነ ሂንዱይዝም ወይም ሌላውም እንድትከተሉት በጥብቅ ስለሚያዝ የእናንተን መመሪያዎች፣ የትክክለኛ መንገድ ፍለጋችሁን ወስዶባችኋል። በመሰረታዊ ደረጃ ህይወታችሁ እንዲኖረው የምትፈልጉትን ትርጉም አሳጥቷችኋል። «እኔ ይህንን ልስጣችሁ ዝግጁ ነኝ። እናንተ ማድረግ ያለባችሁ ያለምንም ጥያቄና መጠራጠር እኔን ማመን ነው። የሚያስፈልገው ነገር በእናንተ በኩል ፍጹም አመኔታ ማሳደር ብቻ ነው» ብሎ ቃል ገብቶላችኋል። አንድ ሰው በራሱ መርምሮ ያላገኘውን ነገር እንዲያምን መጠየቅ ደግሞ የመረዳት ችሎታውን ማሰናከል፣ ተራ አዕምሮ እንዲኖረው ማድረግና ለዘላለም ደደብ ሆኖ እንዲኖር መፍረድ ነው።
297 viewsŻel@lem Ãdineŵ, 07:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 10:54:46 #ይቅርታ
ኃጢኣትን ይቅር የሚል እግዚአብሔር ነው። ታድያ በሉቃ 23፣34 "ኢየሱስም አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ" የሚለው ትርጉሙ ምንድን ነው? የሚል ጥያቄ ይነሳል። ከዚህ ጥቅስ ላይ #አብ #ይቅር ባይ እንደሆነ ይነግረናል። አንዳንዶች ግን ከዚህ ላይ የተገለጠውን የአብን ይቅር ባይነት ተቀብለው ወልድ ይቅር አይልም ወደማለት ድምዳሜ ይሄዳሉ። ትልቅ ስህተት ነው። ከዚህ ጥቅስ ላይ አብ ይቅር እንደሚል ተናገረ እንጂ ወልድ ይቅር እንደማይል የሚናገር ምንም ነገር የለውም።ሌላ ቦታ ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ በማቴ.9፣6 "ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢኣትን ያስተሰርይ ዘንድ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ በዚያን ጊዜ ሽባውን ተነሳ አልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ አለው" ተብሏል።በዚህ ጊዜ አይሁድ ኃጢኣትን ይቅር የሚል እግዚአብሔር ብቻ ነው ብለው አንጎራጉረው ነበር። ሐሳባቸው ትክክል ነው ኃጢኣትን ይቅር የሚል እግዚአብሔር ብቻ ነው። የአይሁድ ትልቁ ችግራቸው ራሱ ክርስቶስ እግዚአብሔር መሆኑን አለመረዳታቸው ነበር። ስለዚህ በዚህኛው ጥቅስ የኢየሱስ ክርስቶስ ይቅር ባይነት ሲጠቀስ በላይኛው ጥቅስ ደግሞ የአብ ይቅር ባይነት ተገልጧል።

ይህንን የመሰለ በክርስቶስ ትንሣኤ ዙሪያም የተነገረ ቃል አለ።ማቴ.27፣63 ላይ ራሱ ክርስቶስ የራሱ አስነሽ እንደሆነ ተነግሯል። በሌላ ቦታ ደግሞ የሐዋ. ሥራ 4፣ 10 ኢየሱስ ክርስቶስን ያስነሳው ሌላ እንደሆነ ተናግሯል ። በትረጓሜያችን ወተንሣእኩ በሥልጣነ ባሕቲትየ በራሴ ሥልጣን ተነሳሁ ቢል አብ አንሥኦ አብ አስነሳው ቢል እና መንፈስ ቅዱስ አንሥኦ ቢል ምንም ዓይነት ተቃርኖ የለም። ሁሉም አንድ ነው። በምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት አካላዊ ግብር እና ሥልጣናዊ ግብር የሚባል አለ። አካላዊ ግብር የሚባለው የአብ መውለድ ማሥረጽ የወልድ መወለድ የመንፈስ ቅዱስ መሥረጽ ነው። ይህ ግብር አይፋለስም። ሥልጣናዊ ግብር የሚባለው ግን ሦስቱ አካላት በኲነታት ተገናዝበው አንዲት ባሕርይ አላቸው ። የዚህች አንዲት ባሕርይ ደግሞ አንዲት ፈቃድ አንዲት ሥምረት አንዲት ክሂል አንዲት ግብረ ባሕርይ አላት። ፈጣሪነት፣ አምላክነት፣ ገዢነት፣ ኃያልነት፣ ይቅር ባይነት እና የመሳሰሉት ግብሮች የአንዲት ባሕርይ ግብራተ ባሕርይ ስለሆኑ ሦስቱም ይጠሩበታል ። አብ አምላክ ይባላል ። ወልድም አምላክ ይባላል። ሮሜ.9፥5፣ መንፈስ ቅዱስም አምላክ ይባላል። ይህንን ስላልን ግን ሦስት አምላክ አንልም። በአንዲት ግብረ ባሕርይ ሦስቱም ተጠሩባት ይባላል እንጂ ። ለዚያ ነው ጠንቅቀን በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ ካልን በኋላ አሐዱ አምላክ እንላለን እንጂ ሠለስቱ አማልክት አንልም ። ነቢየ እግዚአብሔር ምልክአም (ሙሴ) በኦሪት ዘዳግም ስማዕ እስራኤል አሐዱ ውእቱ እግዚአብሔር አምላክከ ብሎ ተናግሯልና።

መጻሕፍት ስለ ክርስቶስ ሲናገሩ ስለ ሰውነቱ በሚናገሩበት ጊዜ መለኮትነቱን ዘንግተው አይደለም። ስለ መለኮትነቱ(ቃልነቱ) ሲናገሩ ሰውነቱን ዘንግተው አይደለም ። ለዚያ ነው ሊቁ ቦ ዘይቤላ መጻሕፍት በእንተ ትስብእቱ ወቦ ዘይቤላ መጻሕፍት በእንተ መለኮቱ ወቦ ዘይቤላ መጻሕፍት በእንተ ትስብእቱ ወበእንተ መለኮቱ ኅቡረ ተብሎ የተገለጠው። ሌላው ጌታችን በመስቀል ላይ ሆኖ አባት የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ያለን ለእኛ አብነት ለመሆን ነው። ጠላትህን ውደድ ብሎ አስተምሮ ነበርና። እርሱም ተመሀሩ እምኔየ እስመ የዋሕ አነ ብሏልና። በተግባር ይቅር ባይነትን ሲያስተምረን ነው። ሊቀ ዲያቆኑ ቅዱስ እስጢፋኖስን ይህን አብነት አድርጎ በድንጋይ ለሚወግሩት ሰዎች ይቅርታን ለምኗል።
288 viewsŻel@lem Ãdineŵ, edited  07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 18:24:21 እውነት
እውነት በሰው ብዛት አትዳኝም። እውነት ሁልጊዜም እውነት ናት። ሰው በእውነት መኖር ሲያቅተው ለውሸቱ ደጋፊ ይፈልጋል። ለውሸቱ የማይገናኝ ጥቅስ ይጠቅሳል ። ውሸትን ግን በሚዲያ ብታስነግራት፣ በመጽሐፍ ብትጽፋት፣ በብዙ ሰው ብታስነግራት ያው ውሸት ናት።ሰው በመንጋ ከማሰብ ወጥቶ በተ ሰጠው አእምሮ ክፉና መልካሙን አመዛዝኖ የሚወስን መሆን ይገባዋል። በውሸት ሚልየን ሕዝብ ከሚያጨበጭብልህ እውነትን ተናግረህ ሚልየን ሰው ቢጠላህ ይሻላል።ሰው ቢጠላህ የእውነት ባለቤት እግዚአብሔር ግን ከአንተ ጋር ይሆናል። ቅዱሳን መላእክቱ ይወዱሃል።

እውነት አንድ ነው።እርሱም እግዚአብሔር ነው ። የእግዚአብሔር ትእዛዙ ሥርዓቱ የእውነት መገለጫ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥም በሌላው ሀገርም ሰላም ፍቅር የሌለበት ምክንያት ሰላም እና ፍቅር እንዲያሸንፉ ሰው ስለማይፈልግ ነው።ለምሳሌ ኢትዮጵያ ውስጥ የእርስ በእርስ ጦርነት የበዛው እውነት እንድታሸንፍ ስለማይፈለግ ነው። እየተጣላንበት ያለው እውነታው አንድ ነው።ነገር ግን እውነታውን ከመቀበል ይልቅ ራስ ወዳድነት እና ግለኝነት ስለተስፋፋ ሁሉም ከፍቅር እና ከአንድነት እሳቤ ወጥቶ ለጦርነት ተሰለፈ።

ፍትሕ፣ፍቅር (ሌላውን እንደራስ መውደድ)፣ አንድነት የእውነት መገለጫዎች ናቸው። ነገር ግን እውነትን የጠሉ ሰዎች ስግብግብነትን፣ ዘረኝነትን እና ማዳላትን ገንዘብ አድርገው ሰውን ያበጣብጣሉ።ዘላቂ ሰላም የሚመጣ በጦርነት አይደለም። በይቅርታና በፍትሕ እንዲሁም በፍቅር እንጂ። እውነትን የሚፈራት ውሸታም ሰው ነው።

በእውነት እንኑር
ለእውነት እንኑር
ለእውነት እንሙት
344 viewsŻel@lem Ãdineŵ, 15:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:41:31 #አሞኛል ብዬ ለመፃፍ በስተት አምሮኛል የሚል Message ልኬላት "እኔም #አምሮኛል " የሚል መልስ ደርሶኝ
°
°
ጨንቆኛል
370 viewsŻel@lem Ãdineŵ, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:41:30 "ቀላል ሴት አድርጋችሁኛል ድንግሌን ለማንም አልሰጥም ብዬ የተቀመጥኩ ሴት ነኝ" ብላ Post አድርጋለች

#ማነሽ_የኔ_እህት ያንቺ ድንግልና የቀበሌ መታወቂያ ነው እንዴ በየአመቱ የሚታደሰው
306 viewsŻel@lem Ãdineŵ, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:41:29 የበላይነት ስሜት መች እንደሚሰማህ ታውቃለህ #Man

ሲኖ ውስጥ ሆነህ #Vits በጎንህ ስታልፍ ነው
322 viewsŻel@lem Ãdineŵ, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:41:28 ኢትዮጵያ የሚባል ምግብ ቤት ገብተህ
ቶሎ ሚደርስ ምግብ ምን አላችሁ ስትላቸው
ግጭት ለብለብ ብሄር ሳይገባበት በሀይማኖት ተፈርሾ
341 viewsŻel@lem Ãdineŵ, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:41:28 አጭጭር ሰዎችን አታበሳጭ
ምክንያቱም
ድንጋይ ለማንሳት ቅርብ ናቸዉ
326 viewsŻel@lem Ãdineŵ, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 20:41:27 አልዋሽም ስበላ አሰብኩሽ

አልዋሽም ስጠጣ አሰብኩሽ
315 viewsŻel@lem Ãdineŵ, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ