Get Mystery Box with random crypto!

Obadiah Apologetics

የቴሌግራም ቻናል አርማ alidashdy — Obadiah Apologetics O
የቴሌግራም ቻናል አርማ alidashdy — Obadiah Apologetics
የሰርጥ አድራሻ: @alidashdy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 384
የሰርጥ መግለጫ

✟ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✟
"የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥"
(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10:5)
📌 ስለ ክርስትና፦ @TheTriune

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-04 00:41:30 ሙስሊሞች ይህን ሲባሉ ከቁርአን በመጥቀስ ነቢያትና ሐዋርያት ሙስሊም መሆናቸውን መስክረዋል ይላሉ

ይህ ግን አሁንም ተቀባይነት የሌለው circular reasoning ነው። ቁርአን የአላህ ቃል ነው። በቁርአኑ እከሌ የሚባለው ነቢይ፥ እከሌ የሚባለው ሐዋሪያ ሙስሊም ነኝ ብሏል ያለው አላህ ነው። እነርሱ ብለዋል ብሎ ተናገረ እንጂ፥ እነርሱ ራሳቸው አይደሉም ሙስሊም ነን ያሉት

ከላይ ባየነው ምሳሌ መሠረት፥ አቶ አማረ "አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አቶ አማረ ምሩቄ ነው ብሏል" ቢል፥ ነገር ግን ከራሱ ከዮኒቨርሲቲው የመጣ ቀዳማዊ ማስረጃ ከሌለው፥ የተናገረው ነገር ተቀባይነት እንደማይኖረው ሁሉ፥ ነቢያትና ሐዋርያት አላህን ማምለካቸውን የሚያሳይ ከራሳቸው ዘንድ የመጣ ቀዳማዊ ማስረጃ ከሌለው ተቀባይነት የለውም።

ሙስሊም መሆናቸው ሊረጋገጥ ካስፈለገ primary source ያስፈልጋል። ራሳቸው ሙስሊም መሆናቸውን መመስከር አለባቸው። እንጂ ጥያቄ ምልክት ውስጥ የገባው አላህ ለራሱ ምስክርነት ሊሰጥ አይችልም። ሙስሊም ለመሆናቸው ከራሳቸው ዘንድ የመጣ ማስረጃ መምጣት አለበት

ታዲያ ነቢያትና ሐዋርያት ያወቁት የእስራኤል አምላክ ማነው?

ነቢያትና ሐዋርያት ያወቁት አንዱ የእስራኤል አምላክ ሥላሴ ነው። አብ፥ ወልድ፥ መንፈስ ቅዱስ። ይህ የነቢያቱና የሐዋርያቱ ጽሑፎች ከሆኑት ቅዱሳት መጻሕፍት ሊረጋገጥ የሚችል ነገር ነው። ከዘፍጥረት ጀምሮ እስከ ራዕይ ድረስ የተመሰከረለት ሀቅ ነው

በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩት ነቢያት አምላካቸው አብ፥ ልጁ/መልአኩ እና መንፈስ ቅዱስ መሆኑን መስክረዋል። አምላካቸው የነበረው አንዱ አምላክ እርሱ ነው። በአዲስ ኪዳንም ሐዋርያት፥ ይህንኑ አምላክ በመከተል አምላካቸው አብ፥ ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስና መንፈስ ቅዱስ መሆኑን መስክረዋል። የነቢያቱ አንዱ አምላክ የነርሱም አምላክ ነበርና። (ልጁ በስጋ ስለመጣ ኢየሱስ ክርስቶስ ተባለ)

የነቢያትና የሐዋርያት አምላክ ሥላሴ ነው። አላህ አይደለም። ይህ ማለት አላህ ጣዖት ነው ማለት ነው። እስራኤል ያላወቀው ባዕድ አምላክ ተብዬ

ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያዘን አንከተለውም። አናመልከውም። አንገዛለትም። አናምንበትም። አንፈራውም። ምንም አይነት ቦታም አንሰጠውም። ይልቁንም እንደ ጣዖት እንርቀዋለን። ሰዎችም እርሱን በማምለክ በጣዖት አምልኮ እንዳይተበተቡ እንጣራለን። የማይታወቅ የአሕዛብ አምላክ ነውና። አይን እያላቸው ከማያዩት፥ ጆሮ እያላቸው ከማይሰሙት ጣዖታት ምድብ የሚመደብ ነው።

እስራኤል ያላወቀውን አምላክ ከመከተል እንጠበቅ!

say #No! to allah!
180 viewsedited  21:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 00:41:30 ሙስሊሞች ጣዖት አምልኮ ሺርክ ብቻ ይመስላቸዋል። ማለትም፥ ለነርሱ ጣዖት አምልኮ ማለት ሌላ አካልን ከአላህ ጋር አጋርቶ ማምለክ ብቻ ይመስላቸዋል። ሺሪክ ማለት በአረብኛ ማጋራት፥ ማሻረክ ማለት ነውና።

ቁርአንም ቢሆን በመሐመድ ዘመን የነበሩ ጣዖት አምላኪያንን የሚከሰው በሺርክ ነው። የጣዖታዊያኑ ጥፋት ከአላህ ጋር ሌሎች አማልክትን አጋርተው ማምለካቸው እንደሆነ ነው የሚናገረው።

ነገር ግን የተሳሳተ የጣዖት አምልኮ አረዳድ ነው። ምክንያቱም ጣዖት አምልኮ፥ ከእውነተኛው አምላክ ጋር ሌላ አካልን አጋርቶ ማምለክ ብቻ አይደለምና

አንድ ሰው አንድን አምላክ ብቻ ሳያጋራ እያመለከ እንኳ ጣዖት አምላኪ ሊሆን ይችላል። ያ የሚያመልከው አንዱ አምላክ ነቢያትና ሐዋርያት ያወቁት የእስራኤል አምላክ ካልሆነ፥ ሳያጋራ ቢያመልከውም እንኳ ጣዖት አምላኪ ከመሆን አይተርፍም። ምክንያቱም ያ የሚያመልከው አምላክ ሀሰተኛ አምላክ ነውና

ሳታጋራ ለብቻው የምታመልከው አምላክ እስራኤል ያላወቀው አምላክ ከሆነ ጣዖት አምላኪ ነህ! (ዘዳ 13:1-4)

አለማጋራትህ ከጣዖት አምላኪነት አያተርፍህም። "አምላኬ የእስራኤል አምላክ ነው ወይ?" የሚለው መሠረታዊ ጥያቄ መመለስ አለበት። ካልሆነ፥ የፈለገ አንድ ቢሆን እንኳ፥ ከጣዖትነት አይተርፍም። አንተም ጣዖት አምላኪ ትባላለህ

ምክንያቱም እውነተኛው አምላክ ነቢያትና ሐዋርያት ያወቁት የእስራኤል አምላክ ነው። እሱን ያልሆነ አምላክ በሙሉ አምላክ አይደለም። ሀሰተኛ አምላክ ነው፥ ጣዖት ነው። አንድ መሆኑ፥ ከጣዖትነት አያተርፈውም

አዎ፥ እውነተኛውን የእስራኤል አምላክ ከሌሎች አካላት ጋር አዳብሎ ማምለክ ጣዖት አምልኮ ነው። ነገር ግን ጣዖት አምላኪነት እርሱ ብቻ አይደለም። በእስራኤል አምላክ ፋንታ ሌላ አምላክን ማምለክም እንዲሁ ጣዖት አምልኮ ነው። ተተኪው አንድ ሊሆን ይችላል፥ ብዙ አማልክት ሊሆኑ ይችላሉ። ነቢያትና ሐዋርያት ያላወቁት የእስራኤል አምላክ ከሆነ፥ አንዱም አምላክ መድበለ አማልክቱም ጣዖት ናቸው

አንድን አምላክ የተባለን ነገር ጣዖት የሚያስብለው፥ የእስራኤልን አምላክ መሆን አለመሆኑ እንጂ ቁጥሩ አይደለም!

በታሪክ ውስጥ አንድን አካል ብቻ ሳያጋሩ በብቸኝነት ያመለኩ ሕዝቦች ነበሩ። ለምሳሌ፦

የግብጹ አቴን፦ የግብፅ ፈርዖን የነበረው አኬናቴን፥ አቴን ይባል የነበረውን አምላክ በብቸኝነት ያመልክ ነበር። እርሱ በነገሰ ሰአትም ሌሎች አማልክት እንዳይመለኩ ከልክሎ ነበር። በዚህም ምክንያት ግብፅ በሙሉ በእርሱ ዘመን አሃዳዊ ነበረች። ያለማጋራት ይህን አምላካቸውን ያመልኩ ነበር

https://en.wikipedia.org/wiki/Aten

ታዲያ! እነዚህ ሕዝቦች ያለማጋራት አንድ አምላክን በብቸኝነት ስላመለኩ ከጣዖት አምላኪነት ይተርፋሉ?

አይተርፉም! ምክንያቱም ያመለኩት አምላክ የእስራኤል አምላክ አይደለም። ሌላ አምላክን ነበር ያመለኩት። በዚህም ምክንያት ጣዖት አምላኪ ናቸው። አንድ አምላክ ማምለካቸው ከጣዖት አምላኪነት አላዳናቸውም!

ያመለኩት ነቢያትና ሐዋርያት ያወቁትን የእስራኤል አምላክ እስካልሆነ ድረስ፥ የፈለገ አንድ አምላክ ቢያመልኩም ጣዖት አምላኪ ናቸው። አምላካቸውም ሀሰተኛ አምላክ ነው። አንድ አምላክ መሆኑ እውነተኛ አምላክ አያደርገውም።

ሙስሊሞች አላህ የሚባል አምላክ አላቸው። አንድ ነው ይላሉ። አንድን አምላክ በብቸንነት በማምለካቸው ከጣዖት አምላኪነት የተረፉ ይመስላቸዋል

ይህ ግን ሀሰት ነው። የእነርሱ አምላክ አላህ ነቢያትና ሐዋሪያት ያወቁት የእስራኤል አምላክ ለመሆኑ ማስረጃቸው ምንድነው? አላህ የነቢያትና የሐዋርያት አምላክ መሆኑን በተጨባጭና ተቀባይነት ባለው ማስረጃ ማረጋገጥ ይችላሉ??? ምክንያቱም አላህ እስራኤል ያላወቀው እንግዳ አምላክ ከሆነ፥ እንደ አቴን የሚሆነው። ስለዚህ አላህ ነቢያትና ሐዋርያት ያወቁት የእስራኤል አምላክ መሆኑ መረጋገጥ አለበት

ቁርአን አላህ የነቢያትና የሐዋርያት አምላክ ነው ስላለ፥ ነው ማለት አይቻልም። ምክንያቱም ቁርአን የራሱ የአላህ ቃል ነው ተብሎ ይታመናልና። ስለዚህ ጥያቄ ምልክት ውስጥ የገባው አላህ ለራሱ ምስክር ሊሆን አይችልም። ይህ circular reasoning ይሆናልና።

አላህ ነቢያትና ሐዋርያት ያወቁት የእስራኤል አምላክ መሆኑ ሊረጋገጥ ካስፈለገ፥ የነቢያቱና የሐዋሪያቱ ጽሑፎች ከሆኑት ቅዱሳት መጻሕፍት (scripture) ነው መሆን ያለበት። ከራሱ ምስክርነት ባሻገር external evidence ያስፈልገዋል። የነቢያቱና የሐዋሪያቱ አምላክ መሆኑ፥ ከራሳቸው ነው መረጋገጥ ያለበት

ለምሳሌ፦ አቶ አማረ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሩቅ ነኝ ካለ፥ የዚያ ዩኒቨርስቲ ምሩቅ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው መመስከር አለበት። እርሱ ከዚያ ዮኒቨርስቲ ለመመረቁ ምስክርነቱና ማስረጃው መምጣት ያለበት ከዩኒቨርስቲው ነው

እንጂ ከዩኒቨርስቲው ምንም አይነት ማስረጃ ሳያመጣ፥ "የዚያ ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ነኝ" ብሎ ስለራሱ ሺህ ጊዜ ቢመሰክር ንግግሩ ተቀባይነት አይኖረውም። የግድ ከራሱ ከዩኒቨርስቲው የዚያ ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ለመሆኑ ማስረጃና ምስክርነት ሊመጣ ይገባል። አስፈላጊ በሆነው መንገድ ሁሉ፥ ራሱ ዩኒቨርስቲው አቶ አማረን እንዳስመረቀው መመስከር አለበት።

የዮኒቨርስቲው ምሩቅ መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃና ምስክርነት ሳያመጣ፥ በራሱ ቃልና ምስክርነት ላይ ብቻ ተመስርቶ "የአዲስ አበባ ዮኒቨርስቲ ምሩቅ ነኝ" ቢል፥ ተቀባይነት አይኖረውም

ልክ እንዲሁ አላህም የነቢያትና የሐዋርያት አምላክ ከሆነ፥ ራሳቸው ነቢያቱና ሐዋርያቱ አላህ አምላካቸው መሆኑን መመስከር አለባቸው። እሱ አምላካቸው መሆኑ ሊረጋገጥ የሚገባው ከእነርሱ ዘንድ በመጣ ምስክርነትና ማስረጃ ነው

እንጂ የእነርሱን ምስክርነትና ማስረጃ ሳያመጣ፥ በራሱ ቃል ብቻ ተመስርቶ "የነቢያትና የሐዋርያት አምላክ ነኝ" ስላለ ብቻ ተቀባይነት አይኖረውም። የግድ የእነርሱ አምላክ ለመሆኑ ከእነርሱ ዘንድ በመጣ ማስረጃ መረጋገጥ አለበት። እነርሱ ያላወቁትን አምላክ አትከተሉ ተብለናልና

ነገር ግን አላህ ነቢያትና ሐዋርያት ያወቁት አንዱ የእስራኤል አምላክ ካልሆነና፥ አንዱ የነቢያትና የሐዋርያት አምላክ ሌላ አምላክ መሆኑ ከተረጋገጠ...#አላህ_ጣዖት_ነው_ማለት_ነው!

ከራሳቸው ከነቢያትና ከሐዋርያት በመጣ ማስረጃ፥ እነርሱ ያወቁትና የተከተሉት አንዱ አምላክ የሙስሊሞች አምላክ አላህ አለመሆኑ ከተረጋገጠ አላህ ጣዖት ነው ማለት ነው። እስራኤል ያላወቀው እንግዳ አምላክ ነው ማለት ነው። ስለዚህ ልንጸየፈውና ልንርቀው ይገባል

በግልጽ እስራኤል ካወቀው፥ ነቢያትና ሐዋርያት ከተከተሉት አምላክ ውጪ ሌላን አምላክ እንዳንከተልና እንዳናመልክ መጽሐፍ ቅዱስ ያዘናል። ይህ የጸና እና የታመነ ምስክርነት ነው። አላህ ይህ እስራኤል ያወቀውና የተከተለው አምላክ ካልሆነ ጽዩፍ ጣዖት ነው

ለሺህ አመታት በቅብብሎሽ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው የብዙ ነቢያትና ሐዋርያት ቃል፥ በአንድ ነቢይ ነኝ ባይ ቃል ሊሻር አይችልም። ለሺህ አመታት በቅብብሎሽ የወረደው የነቢያትና የሐዋርያት ቃል የእግዚአብሔር ቃል ሲሆን ምስክርነቱ የጸና ነው። ስለዚህ የአንድ ነቢይ ተብዬ ቃል ይህን ሁሉ ምስክርነትና ሀቅ ሊቀለብስ አይችልም
51 viewsedited  21:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 14:15:43 Argument from silence! ሙስሊሞች በብዛት ይህንን ጥያቄ ይጠይቃሉ። ለዚህ ጥያቄያቸው ምላሽ የሚሆኑ ሌሎችም በዚህ የዩትዩብ ቻናል ላይ ተመልሰዋል። ይህንን ቪድዮ እስከ መጨረሻው ስትሰሙት በጽሁፍም የተብራራውን የተስፋዬ ሮበሌን መልስ ታገኛላችሁ። ስለዚ ክርስቲያኖችም ሁኑ ሙስሊሞች ከዚህ ቪድዮ በኋላ ጥያቄ እንደማታነሱ ተስፋ አደርጋለው። አይኔን ግንባር ያድርገው ጆሮዬንም በጥጥ ይድፈነው ካላላችሁና የህሊናችሁን ወቀሳ አልሰማም ካላላችሁ በቀር መረዳት ያለባችሁ የመጨረሻ ነገር ይህ ነው። ስላዳመጣችሁት ተባረኩ!!

ሙስሊሞች ለኡስታዞቻችሁ Share አድርጉላቸው። ክርስቲያኖች ደሞ ለክርስቲያኖች፣ እንዲሁም ሙስሊም ጓደኞች ያላችሁ ደሞ ለጓደኞቻችሁ Share አድርጉላቸው። ቻናሉንም SUBSCRIBE በማድረግ ይህንን የወንጌል ስርጭት አገልግሎት ደግፉ።



78 views11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 11:41:46 "እንዲህም አሉ። እናንተ ሰዎች፥ ይህን ስለ ምን ታደርጋላችሁ? እኛ ደግሞ እንደ እናንተ የምንሰማ ሰዎች ነን፥ ከዚህም ከንቱ ነገር #ሰማይንና #ምድርን ባሕርንም በእነርሱም ያለውን #ሁሉ ወደ #ፈጠረ ወደ ሕያው #እግዚአብሔር ዘወር ትሉ ዘንድ ወንጌልን እንሰብካለን።"
(የሐዋርያት ሥራ 14:15)

" #ዓለሙንና በእርሱ ያለውን #ሁሉ #የፈጠረ #አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም፤"
(የሐዋርያት ሥራ 17:24)

"ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ። ጌታችንና #አምላካችን ሆይ፥ አንተ #ሁሉን #ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረውማልና ክብር ውዳሴ ኃይልም ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት አክሊላቸውን ያኖራሉ።"
(የዮሐንስ ራእይ 4:10-11)

" #ሁሉ ከእርሱና #በእርሱ ለእርሱም #ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።"
(ወደ ሮሜ ሰዎች 11:36)

መጽሐፍ ቅዱስ በግልፅ ሁሉን ፍጥረት የፈጠረው እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ ያስተምራል። ፍጡር አብሮት ፈጠረ የሚል አስተምህሮ ለመጽሐፍ ቅዱስ ባዕድ ነው።

በመጀመሪያ የነበረውም ቃል "ሁሉ በእርሱ ሆነ" መባሉ፥ እውነተኛው አምላክ መሆኑን በማያሻማ መልኩ ያረጋግጣል። እውነተኛው አምላክ ባይሆን ኖሮ፥ ሁሉን መፍጠር ባልቻለ ነበር። ይህ፥ ቃል ፍጡር ሳይሆን እግዚአብሔር መሆኑን ከምንም በላይ ያረጋግጣል።

የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ሁሉን የፈጠረው ፈጣሪ መሆኑ በዮሐ 1:1-3 ላይ ብቻ የተነገረ እውነት አይደለም። ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችም እንደሚያረጋግጡት፥ ልጁ/ቃል የሁሉ ፈጣሪ ነው

"13-14፤ እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ #ልጅ መንግሥት አፈለሰን። 15-16፤ እርሱም የማይታይ አምላክ #ምሳሌ ነው። የሚታዩትና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ #በሰማይና #በምድር ያሉት #ሁሉ በእርሱ #ተፈጥረዋልና ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኵር ነው። #ሁሉ #በእርሱና ለእርሱ #ተፈጥሮአል። 17፤ እርሱም ከሁሉ በፊት ነው #ሁሉም በእርሱ #ተጋጥሞአል።"
(ወደ ቆላስይስ ሰዎች ምዕራፍ 1:13-17)

"2፤ ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም #ዓለማትን #በፈጠረበት #በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤ 3፤ እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ #ምሳሌ ሆኖ፥ #ሁሉን በስልጣኑ #ቃል #እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤"
(ወደ ዕብራውያን ምዕራፍ 1:2-3)

"ለእኛስ ነገር ሁሉ ከእርሱ የሆነ እኛም ለእርሱ የሆንን አንድ አምላክ አብ አለን፥ ነገር #ሁሉም #በእርሱ በኩል #የሆነ እኛም በእርሱ በኩል የሆንን አንድ ጌታ #ኢየሱስ #ክርስቶስ አለን።"
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 8:6)

"8፤ ይላል፤ ስለ #ልጁ ግን። #አምላክ ሆይ፥ ዙፋንህ እስከ ዘላለም ድረስ ይኖራል፤ የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው። 9፤ ጽድቅን ወደድህ ዓመፅንም ጠላህ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ ከጓደኞችህ ይልቅ በደስታ ዘይት ቀባህ 10፤ ይላል። ደግሞ። #ጌታ #ሆይ፥ አንተ ከጥንት #ምድርን #መሠረትህ፥ #ሰማዮችም #የእጆችህ #ሥራ #ናቸው፤ 11፤ እነርሱም ይጠፋሉ አንተ ግን ጸንተህ ትኖራለህ፤ ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃሉ፥ 12፤ እንደ #መጎናጸፊያም #ትጠቀልላቸዋለህ ይለወጡማል፤ አንተ ግን አንተ ነህ፥ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም"
(ወደ ዕብራውያን ምዕራፍ 1:8-12)

ስለዚህ የይሖዋ ምስክር ወገኖቻችን ተሳስተዋል። በዮሐንስ 1:1-3 ላይ የተተረከው ቃል ፍጡር አይደለም። ፍጡር አለመሆኑን ከሚያረጋግጡት ብዙ ማስረጃዎች መካከል ከላይ የተመለከትናቸው ተጠቃሽ ናቸው። ሁሉም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎች እንደሚያረጋግጡት፥ ቃል ፈጣሪ እንጂ ፍጡር አይደለም።

1) ሁሉ በቃል ከተፈጠረና፥ ከተፈጠረው ሁሉ ያለ ቃል የተፈጠረ ከሌለ፥ እንዴት ቃል ራሱ ፍጡር ሊሆን ይችላል? ራሱን ፈጠረ ማለት ነው?

2) መጽሐፍ ቅዱስ #ሁሉን የፈጠረው እግዚአብሔር ብቻ መሆኑን እየተናገረ፥ እንዴት ፍጡር ሁሉ ሊፈጥር ይችላል? ፍጡር ሁሉን ፈጠረ የሚል አስተምህሮ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አለ?

ትክክለኛውን የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ አውቃችሁ ወደ እውነት ትመጡ ዘንድ የዘወትር ጸሎታችን ነው

ጌታ ይርዳን!
346 views08:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 11:41:45 የይሖዋ ምስክሮችና ዮሐንስ 1:1-3

የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 1:1-3 አተረጓጎም በተመለከተ የይሖዋ ምስክሮች እጅግ ብዙ ስህተቶች አሏቸው። ይህን ክፍል ሲተረጉሙት፥ ቃል እግዚአብሔር መሆኑን በመካድ፥ መለስተኛ አምላክ ወይንም a god በማለት ተርጉመውታል

ይህ እጅግ ብዙ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ነው። "መለስተኛ አምላክ ብሎ ነገር አለ ወይ? እግዚአብሔር ብቻዬን ነኝ አላለም እንዴ? ፍጡራን በተባሉበት አውድ ነው ቢባል እንኳ፥ የትኛው ፍጡር ነው ከፍጥረት በፊት የነበረው?" የሚሉ እጅግ ብዙ ዘርፈ ብዙ ጥያቄዎችን ያስነሳል

ዛሬ እግዚአብሔር ቢፈቅድ፥ ይህንኑ የተሳሳተ አተረጓጎማቸውን፥ በእግዚአብሔር ቃል አስተምህሮ ለመዳሰስ እንሞክራለን፦

1) ቃል የሁሉ ፈጣሪ ነው

የዮሐንስ ወንጌል በቀጥታ ከሚናገራቸው ነገሮች መካከል አንዱ፥ ቃል ሁሉ ፈጣሪ መሆኑን ነው

"1፤ በመጀመሪያው #ቃል ነበረ፥ #ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ #ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። 2፤ ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። 3፤ #ሁሉ #በእርሱ #ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም።"
(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 1:1-3)

ይህ ማለት፥ የተፈጠረ ማንኛውም ነገር በሙሉ የተፈጠረው በቃል ነው ማለት ነው። ሁሉም ፍጥረት የተፈጠረው በቃል መሆኑን፥ ዮሐ 1:3 ቃል በቃል ይናገራል። ይህ ለቃል ፈጣሪነት የማይታበል ምስክርነት ነው። ከዚያም አልፍ ተርፎ፥ ከሆነው ሁሉ አንዳች ያለ እርሱ እንዳልሆነ ግልጽ ያደርጋል

"ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ #ከሆነውም #አንዳች ስንኳ ያለ #እርሱ #አልሆነም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1:3)

ከሆነውም እንኳ አንዳች ያለ እርሱ አልሆነም ማለት ከተፈጠረው ሁሉ አንዳች ያለ እርሱ አልሆነም ማለት ነው። "ከሆነው" ማለት ከተፈጠረው ማለት ነው። ካለመኖር ወደ መኖር የመጣ ነገር ሁሉ የሆነ ወይንም የተፈጠረ ይባላል። ከሆነው/ከተፈጠረው #አንዳች ያለ ቃል አልሆነም። ማለትም፥ ያለ ቃል አልተፈጠረም። ይህ ማለት፥ ቃል ያልፈጠረው ፍጡር የለም ማለት ነው። ፍጡር የሆነ ነገር በሙሉ የተፈጠረው በቃል ሲሆን፥ ፍጡር ሆኖ ሳለ ቃል ያልፈጠረው ምንም እንደሌለ በግልጽ ቃሉ ያስተምራል

የይሖዋ ምስክሮች፥ ልክ እንደ ክርስቲያኖች፥ ቃል የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ይቀበላሉ። በመጀመሪያ ቃል ነበር ሲል፥ እየተናገረ ያለው ስለ ወልድ መሆኑን ያምናሉ። ነገር ግን ይህ የእግዚአብሔር ልጅ፥ ፍጡር ነው ብለው ያምናሉ።

በመጀመሪያ የነበረው ቃል ፍጡር ከሆነ፥ ራሱን ፈጥሯል ማለት አይሆንም ወይ?

ዮሐ 1:3 ቃል በቃል እንደሚናገረው፥ ሁሉ የተፈጠረው በቃል ነው። ከዚያም ነገሩን በይበልጥ ሲያጠብቀው፥ ከሆነው/ከተፈጠረው ሀሉ አንዳች ያለ እርሱ አልሆነም/አልተፈጠረም በማለት ፍጡር የተባለ ነገር ሁሉ የተፈጠረው በቃል መሆኑን ይመሰክራል። ቃል ያልፈጠረው ፍጡር የለም። የትኛውም ፍጡር የሆነ ነገር፥ ያለ ቃል አልተፈጠረም።

ይህ ማለት ቃል ፍጡር ከሆነ፥ ራሱን ፈጠረ ማለት ነው!

ዮሐ 1:3 ግልፅ እንደሚያደርገው፥ ቃል ያልፈጠረው ፍጡር የለም። ስለዚህ ቃል ራሱ ፍጡር ከሆነ፥ ራሱን ፈጥሯል ማለት ነው። ፍጡር ሆኖ በቃል ያልተፈጠረ የለምና። በምንም አይነት መንገድ፥ "ቃል ፍጡር ነው፥ ነገር ግን ያለ እርሱ የተፈጠረ ፍጡር የለም" ማለት አይቻልም። ሁሉ ፈጥሯል፥ ከተፈጠረው ያለ እርሱ የተፈጠረ የለም እስከተባለ ድረስ፥ እርሱ ራሱ ፍጡር ነው ከተባለ፥ ራሱን ፈጥሯል ማለት ነው

ይህ ደግሞ ኢ-አመክንዮአዊ ነው። አንድ አካል ራሱን ሊፈጥር አይችልም። ለመፍጠር በሕልውና መኖር አለበት። መፈጠር ካስፈለገው ደግሞ በሕልውና የለም ማለት ነው። ስለዚህ ራሱን ፈጠረ ሊባል አይችልም። ኢ-አመክንዮአዊ ግጭት ነውና። ኢ-አመክንዮአዊ ግጭት ያለበት አቋም ደግሞ እውነት ሊሆን አይችልም። ይህ ማለት ቃል ፍጡር ሊሆን አይችልም ማለት ነው።

ቃል የሁሉ ፈጣሪና፥ ከተፈጠረው ያለ እርሱ አንዳች ያልተፈጠረው ፈጣሪ ሊሆን የሚችለው እርሱ ራሱ ፍጡር ካለሆነ ነው። ዘላለማዊው ፈጣሪ ከሆነ ብቻ ነው፥ ሁሉን ፍጥረት ሊፈጥር የሚችለው። ፍጡር ስላልሆነ፥ ከሆነው ያለ እርሱ አንዳች አልሆነም ተብሎለታል። ምክንያቱም የእርሱ ምድብ "ከሆነው" ውስጥ አይደለም። እርሱ የ"ነበረ" ነው። ቃል የነበረ እንጂ የሆነ ስላልሆነ፥ ከሆነው ያለ እርሱ አንዳች አልሆነም ተባለለት።

➣ ይህ ቃል ፍጡር ነው የሚለው እምነት ስህተት መሆኑን ያረጋግጣል

ሌላው አስፈላጊ ነጥብ፥ በዮሐ 1:3 ላይ ሁሉ በቃል እንደሆነ ይናገራል። መጽሐፍ ቅዱሳችንን ስናጠና፥ ፍጥረትን ሁሉ የፈጠረው እውነተኛው አምላክ እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ እንረዳለን። የሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ብቻ ስለሆነ፥ ፍጡር ፍጥረትን ፈጠረ ማለት አይቻልም። መጽሐፍ ቅዱስ አንድም ቦታ ላይ፥ ፍጡር የፍጥረት ሁሉ ፈጣሪ ነው አይልም። የፍጥረት ሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ብቻ ነውና። ስለዚህ ቃል ሁሉን ፈጥሯል መባሉ፥ እውነተኛው አምላክ እንጂ አነስተኛ አምላክ የሆነ ፍጡር ላለመሆኑ ማስረጃ ነው።

"የያዕቆብ እድል ፈንታ እንደ እነዚህ አይደለም፤ #እርሱ #የሁሉ #ፈጣሪ ነውና፤ እስራኤልም የርስቱ ነገድ ነውና፤ #ስሙ የሠራዊት ጌታ #እግዚአብሔር ነው።"
(ትንቢተ ኤርምያስ 10:16)

"የያዕቆብ እድል ፈንታ እንደ እነዚህ አይደለም፥ #እርሱ #የሁሉ #ፈጣሪ ነውና፤ እስራኤልም የርስቱ ነገድ ነው፥ #ስሙም የሠራዊት ጌታ #እግዚአብሔር ነው።"
(ትንቢተ ኤርምያስ 51:19)

"ከማኅፀን የሠራህ፥ የሚቤዥህ #እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ። #ሁሉን #የፈጠርሁ፥ ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤ ከእኔ ጋር ማን ነበረ?"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 44:24)

"እርሱም #ሰማይንና #ምድርን #ባሕርንም፥ በእነርሱ ያለውንም #ሁሉ #የፈጠረ፤ እውነትን ለዘላለም የሚጠብቅ፤"
(መዝሙረ ዳዊት 146:6)

"1፤ #እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። #ሰማይ ዙፋኔ ነው፥ #ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? የማርፍበትስ ስፍራ ምንድር ነው? 2፤ እነዚህን #ሁሉ እጄ #ሠርታለችና እነዚህ ሁሉ የእኔ ናቸው ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን ወደዚህ ወደ ትሑት፥ መንፈሱም ወደ ተሰበረ፥ በቃሌም ወደሚንቀጠቀጥ ሰው እመለከታለሁ።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 66:1-2)

"አንተ ብቻ #እግዚአብሔር ነህ፤ ሰማዩንና #የሰማያት_ሰማይን ሠራዊታቸውንም #ሁሉ፥ #ምድሩንና በእርስዋ ላይ ያሉትን #ሁሉ፥ ባሕሮቹንና በእነርሱ ውስጥ ያለውን #ሁሉ፥ #ፈጥረሃል፥ ሁሉንም ሕያው አድርገኸዋል፤ የሰማዩም ሠራዊት ለአንተ ይሰግዳሉ።"
(መጽሐፈ ነሀምያ 9:6)

"ፍለጋ የሌለውን የክርስቶስን ባለ ጠግነት ለአሕዛብ እሰብክ ዘንድ፥ #ሁሉንም #በፈጠረው #በእግዚአብሔር ከዘላለም የተሰወረው የምሥጢር ሥርዓት ምን እንደሆነ ለሁሉ እገልጥ ዘንድ ይህ ጸጋ ከቅዱሳን ሁሉ ይልቅ ለማንስ ለኔ ተሰጠ፤"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 3:8-9)

"እነርሱም በሰሙ ጊዜ በአንድ ልብ ሆነው ወደ #እግዚአብሔር ድምፃቸውን ከፍ አደረጉ እንዲህም አሉ። ጌታ ሆይ፥ አንተ #ሰማዩንና #ምድሩን ባሕሩንም በእነርሱም የሚኖረውን #ሁሉ #የፈጠርህ፥"
(የሐዋርያት ሥራ 4:24)
241 views08:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 20:11:40 ሰሞኑን በወለጋ በደረሰው ጭፍጨፋ ከ1,500 በላይ ወገኖቻችን በግፍ መጨፍጨፋቸው ተሰምቷል

እግዚአብሔር የወገኖቻችንን ቤተሰቦችና ወዳጆች፥ እኛንም እንዲያጽናና ወንጀለኞቹ ላይም እንዲፈርድ አጥብቀን እንማፀነዋለን!

"ሐሰትን የሚናገሩትን ታጠፋቸዋለህ፤ #ደም #አፍሳሹንና ሸንጋዩን ሰው እግዚአብሔር #ይጸየፋል።"
(መዝሙረ ዳዊት 5:6)

"አሕዛብ፥ አምላካቸው ወዴት ነው? እንዳይሉ፥ የፈሰሰውን የባሪያዎችህን #ደም #በቀል በዓይኖቻችን ፊት አሕዛብ ያወቁ፤"
(መዝሙረ ዳዊት 79:10)
241 views17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 20:10:55 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመለኮት ብቻ የሆኑ ባህሪያት እንዳሉት በመናገር አምላክ መሆኑን ተናግሯል። የትኛውም ፍጡር እነዚህ ባህሪያት ሊኖሩት ስለማይችሉ፥ ክርስቶስ እነዚህ ባህሪያት እንዳሉት መናገሩ ሊስተባበል በማይችል መልኩ አምላክነቱን መግለፁን ያረጋግጣል። ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ጌታ ኢየሱስ አምላክ መሆኑን አያስተምርም ብሎ መከራከር አይቻልም

ክርስቶስ በዚህ መልኩ አምላክነቱን ከገለፀባቸው ቦታዎች መካከል፥ ጥቂቱን ለመመልከት እንሞክር፦

"ኢየሱስም። እኔ መንገድና እውነት #ሕይወትም #ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 14:6)

"ኢየሱስም። ትንሣኤና #ሕይወት እኔ #ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤"
(የዮሐንስ ወንጌል 11:25)

በዚህ ቦታዎች፥ ጌታ ኢየሱስ መንገድ፥ እውነትና ሕይወት መሆኑን ሲናገር እንመለከታለን። "ሕይወት ነኝ" ማለቱ የሰው ልጆች ሕይወት መሆኑንና፥ ለሚያምኑበት ሁሉ የዘላለም ሕይወት ምንጭ መሆኑን ያመለክታል። ለሚያምኑበት ሰዎች የዘላለም ሕይወት መስጠቱ፥ እርሱን የእነርሱ ሕይወትና የሕይወት ምንጭ ያደርገዋል።

በመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ፥ ለሰው ልጆች ሕይወትና የሕይወት ምንጭ የሆነው እግዚአብሔር ብቻ መሆኑን እንረዳለን፦

" #እግዚአብሔርም ለአባቶችህ ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም እንዲሰጣቸው በማለላቸው በምድሪቱ ትቀመጥ ዘንድ፥ #እርሱ #ሕይወትህ የዘመንህም ርዝመት #ነውና አምላክህን እግዚአብሔርን ትወድደው ትጠባበቀውም ቃሉንም ትሰማ ዘንድ ምረጥ።"
(ኦሪት ዘዳግም 30:20)

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረው፥ ለሕዝቡ የሕይወት ምንድን የሆነው እግዚአብሔር ነው። በታሪክ የትኛውም ፍጡር "እኔ ሕይወት ነኝ" ብሎ አያውቅም፥ ሊልም አይችልም።

ሲቀጥል፥ መጽሐፍ ቅዱስ ለሰዎች ሕይወት የሚሰጠውና፥ ሰዎችን በሕይወት የሚያኖረው እግዚአብሔር መሆኑን ይናገራል

"እንደ ዛሬም #በሕይወት #እንዲያኖረን፥ ሁልጊዜም መልካም እንዲሆንልን፥ አምላካችንን #እግዚአብሔርን እንፈራ ዘንድ፥ ይህችንም ሥርዓት ሁሉ እናደርግ ዘንድ እግዚአብሔር አዘዘን።"
(ኦሪት ዘዳግም 6:24)

"39፤ አሁንም እኔ ብቻዬን እኔ እንደ ሆንሁ፥ ከእኔም በቀር አምላክ እንደሌለ እዩ፤ እኔ እገድላለሁ፥ #አድንማለሁ (make alive)፤ እኔ እመታለሁ፥ እፈውስማለሁ፤ ከእጄም የሚያድን የለም።"
(ኦሪት ዘዳግም ምዕራፍ 32:39)

" #እግዚአብሔር ይገድላል #ያድናልም (makes alive)፤ ወደ ሲኦል ያወርዳል፥ ያወጣል።"
(መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2:6)

በነዚህ ቦታዎች ሁሉ ለሰዎች ሕይወት የሚሰጠውና፥ ሰዎችን ሕያው የሚያደርገው እግዚአብሔር እንደሆነ እንረዳለን። በዘዳ 32:39 እና በ1 ሳሙ 2:6 ላይ "አድናለሁ" የሚለው የዕብራይስጥ ቃል ቃል "አኽያህ/אחיה" ሲሆን "ሕያው ማድረግ፥ በሕይወት ማኖር" ማለት ነው። ይህ እግዚአብሔር ብቻ የሚያደርገው ተግባር ነው

ክርስቶስ ደግሞ ዘላለማዊ ሕይወትን የሚሰጠው፥ እርሱ መሆኑን በግልፅ ተናግሯል፦

" #እኔም #የዘላለም #ሕይወትን #እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 10:28)

" አብ ሙታንን እንደሚያነሣ ሕይወትም እንደሚሰጣቸው፥ እንዲሁ #ወልድ ደግሞ ለሚወዳቸው #ሕይወትን #ይሰጣቸዋል።"
(የዮሐንስ ወንጌል 5:21)

"ነገር ግን #ሕይወት #እንዲሆንላችሁ ወደ #እኔ ልትመጡ አትወዱም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 5:40)

"ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ። አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ #የዘላለምን #ሕይወት #ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው።"
(የዮሐንስ ወንጌል 17:1-2)

ክርስቶስ ለሰዎች ሕይወትን የሚሰጠው እርሱ መሆኑን፥ እርሱ ራሱም ሕይወት መሆኑን መናገሩ፥ አምላክ መሆኑን እንደተናገረ ያረጋግጣል

"ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፥ #ወልድንም ማን እንደ ሆነ ከአብ በቀር #የሚያውቅ #የለም፥ አብንም ማን እንደ ሆነ ከወልድ በቀር ወልድም ሊገልጥለት ከሚፈቅድ በቀር የሚያውቅ የለም አለ።"
(የሉቃስ ወንጌል 10:22)

"ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፤ ከአብ በቀር #ወልድን #የሚያውቅ #የለም፥ ከወልድም በቀር ወልድም ሊገለጥለት ከሚፈቅድ በቀር አብን የሚያውቅ የለም።"
(የማቴዎስ ወንጌል 11:27)

በነዚህ ቦታዎችም፥ ጌታ ኢየሱስ ከአባቱ በቀር ማንም እንደማያውቀው ሲናገር እንመለከታለን። ይህ ማለት ፈጽሞ በማንም ሊታወቅ የማይችል የማይመረመር ባህርይ አለው ማለት ነው። ምንነቱ ፈጽሞ በፍጡራን ሊመረመር ስለማይችል፥ መለኮት ከሆነው አብ በቀር እርሱን የሚያውቀው የለም። ክርስቶስ ስለ ራሱ ይህን መናገሩ አምላክ መሆኑን መናገሩን ያረጋግጣል

ምክንያቱም፥ የትኛውም ፍጡር የማይመረመር ባህርይ የለውምና። የትኛውም ፍጡር እንዲህ ተናግሮ አያውቅም፥ ሊናገርም አይችልም። ሲቀጥል፥ ይህን በተናገረበት ቦታ ላይ፥ አብን ማንም እንደማያውቀው ተናግሯል። ይህ አይመረመርነት የመለኮት ባህርይ መሆኑን ያረጋግጣል። አብ ፍጹም እግዚአብሔር በመሆኑ፥ ማንም አያውቀውም።

ክርስቶስ ልክ እንደ አብ፥ እርሱ ወልድ ማንም እንደማያውቀው መናገሩ፥ አምላክ መሆኑን እንደተናገረ ያረጋግጣል። አብ ከመታወቅ በላይ መሆኑን በገለፀበት በዚያው አውድ፥ እርሱም ከመታወቅ በላይ መሆኑን ተናግሯልና

መጽሐፍ ቅዱስም ይህን በይበልጥ በማጽናት፥ ከመታወቅ በላይ የሆነው እግዚአብሔር እንደሆነ ያረጋግጣል፦

"እነሆ፥ #እግዚአብሔር ታላቅ ነው፥ እኛም #አናውቀውም።"
(መጽሐፈ ኢዮብ 36:26)

"ወይስ ሁሉን የሚችል #አምላክ ፈጽመህ #ልትመረምር ትችላለህን?"
(መጽሐፈ ኢዮብ 11:7)

" #እውቀትህ ከእኔ ይልቅ #ተደነቀች፤ በረታች፥ ወደ እርስዋም #ለመድረስ #አልችልም።"
(መዝሙረ ዳዊት 139:6)

"ወደ ሰማይ የወጣ የወረደስ ማን ነው? ነፋስንስ በእጁ የጨበጠ ማን ነው? ውኃንስ በልብሱ የቋጠረ ማን ነው? የምድርን ዳርቻ ሁሉ ያጸና ማን ነው? ይህን ታውቅ እንደ ሆንህ፥ #ስሙ #ማን #የልጁስ ስም #ማን ነው?"
(መጽሐፈ ምሳሌ 30:4)

መጽሐፍ ቅዱስ በግልፅ ከመታወቅ በላይ እግዚአብሔር ብቻ መሆኑን እያስተማረ፥ ክርስቶስ ከመታወቅ በላይ መሆኑን መናገሩ፥ አምላክ መሆኑን እንደተናገረ በግልፅ ያሳያል

ከላይ እንዳልነው፥ ፍጡር በፍጹም ሊኖረው የማይችለውን ባህርይ እንዳለው መናገሩ ክርስቶስ አምላክ መሆኑን ለመናገሩ ሊስተባበል የማይችል ማሳያ ነው። አለኝ ያለው እግዚአብሔር ብቻ ያለውን ባህርይ ነውና
275 viewsedited  17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-18 23:31:28 የቻናላችን ስም ወደ "Obadiah Apologetics" ተለውጧል!
206 views20:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-11 11:54:15 "20፤ በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ #መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ። 21፤ በፊቱ ተጠንቀቁ፥ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ #ኃጢአት ብትሠሩ #ይቅር #አይልምና አታስመርሩት።"
(ኦሪት ዘጸአት ምዕራፍ 23:20-21)

ይህ ክፍል እግዚአብሔር በሲና ተራራ ተገልጦ፥ በእስራኤል ሕዝብ ፊት እንዲሄድ መልአክን እንደሚልክ የተናገረበት ክፍል ነው። በዚህ መልአክ/መልእክተኛ ፊት እንዲጠነቀቁ ይነግራቸዋል። ስሙ በውስጡ ነውና፥ ኀጢአታቸውን ይቅር አይልም

➣ በመላው መጽሐፍ ቅዱስ፥ ኀጢአትን ይቅር አይልም የተባለለት እግዚአብሔር ብቻ ነው፦

"የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፤ #እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን #ከበደል #አያነጻውምና።"
(ኦሪት ዘጸአት 20:7)

"ኢያሱም ሕዝቡን። እርሱ ቅዱስ አምላክ ነውና፥ እርሱም ቀናተኛ አምላክ ነውና #እግዚአብሔርን ማምለክ አትችሉም፤ መተላለፋችሁንና #ኃጢአታችሁን #ይቅር #አይልም።"
(መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 24:19)

ተጓዳኝ አንቀጾች፦ ዘኁ 14:18 ዘዳ 5:11 ዘጽ 34:7

እግዚአብሔር ኀጢአትን ይቅር አይልም ማለት ጨካኝ ነው ወይንም ይቅር የማለት ስልጣን የለውም ማለት አይደለም። በኀጢአት ጉዳይ ስልጣን አለው ማለት ነው። የመማርም ያለመማርም ስልጣን አለው ማለት ነው። በዚያ ጉዳይ ስልጣን ስላለው፥ ሰዎችን በኀጢአታቸው ሊፈርድባቸው ወይንም ይቅር ሊላቸው ስልጣን አለው ማለት ነው። "ኀጢአትን ይቅር አይልም" ማለት ያ ነው።

መልአኩ የእግዚአብሔር ስም/መለኮት በውስጡ ስለሆነ፥ ልክ እንደ እግዚአብሔር ኀጢአትን ይቅር አይልም

ማለትም፥ የኀጢአትን ጉዳይ በተመለከተ ስልጣን አለው ማለት ነው። ልክ እንደ እግዚአብሔር ያሻውን የመማር ያሻውን የመቅጣት ስልጣን አለው። ልክ እንደ አባቱ የሰዎችን ኀጢአት የመቁጠር ሆነ የማስወገድ ስልጣን አለው። የእግዚአብሔር ስም/ባህርይ የእርሱም ነውና፥ ይህ ልዩ የመለኮት ስልጣን አለው። እርሱ ራሱ መለኮት ነውና

መልአኩ፥ በኀጢአት ላይ ያለውን ስልጣን ሲጠቀም እንመለከታለን። ማለትም፥ ኀጢአትን ይቅር ሲል እንመለከታለን።

“ #መልአኩም ከፊቱ ቆመው የነበሩትን፣ “ያደፉ ልብሶቹን አውልቁለት” አላቸው። ኢያሱንም፣ “እነሆ፤ #ኀጢአትህን ከአንተ #አስወግጃለሁ፤ ጥሩ ልብስም አለብስሃለሁ” አለው።”
ዘካርያስ 3፥4 (አዲሱ መ.ት)

ልክ እንደ እግዚአብሔር ኀጢአትን ይቅር ማለቱ፥ የእውነትም የኀጢአት ጉዳይ የሚመለከተው አምላክ መሆኑን ያረጋግጣል። በዘካ 3:4 የምንመለከተው ነገር፥ በዘጽ:23:20-21 ላይ እግዚአብሔር አለው ያለውን ስልጣን በተግባር ሲተገብረው ነው። ይህ መልአኩ ኀጢአትን ይቅር የሚለው አምላክ መሆኑን ያረጋግጣል

በሐዋ 7:60 ግን እስጢፋኖስ ክርስቶስን ኀጢአታቸውን እንዳይቆጥር በመለመን፥ ኢየሱስ ኀጢአትን የመቁጠርና ያለመቁጠር ስልጣን ያለው አምላክ መሆኑን መስክሯል።

ይህ ክርስቶስ ያ ለሙሴ የተገለጠው መልአክ፥ እግዚአብሔርም "ኀጢአታችሁን ይቅር አይልም" ያለለት መልአክ/መልእክተኛ መሆኑን ከምንም በላይ ያረጋግጣል።

መልአኩ ልክ እንደ ክርስቶስ ከአብ የተለየ መለኮታዊ አካል መሆኑን በመሰከረበት አውድ፥ ክርስቶስ ኀጢአትን በተመለከተ ስልጣን እንዳለው መስክሯል። ምክንያቱም ክርስቶስ ያ በዘጽ 23:21 የተነገረለት መልአክ ነውና። በዘጽ 23:20-21 መልአኩ አለው የተባለውን ብቸኛ የመለኮት ስልጣን አለው። ይህ እስጢፋኖስ ኢየሱስ ለሙሴ የተገለጠለት መልአክ/መልእክተኛ መሆኑን እንደመሰከረ በማያሻማ መልኩ ያረጋግጣል

ጌታ ይርዳን!
248 views08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-11 11:54:15 እግዚአብሔር በመልአኩ አማካኝነት ስራውን መስራቱ፥ እግዚአብሔርና መልአኩ የተለያዩ አካላት መሆናቸውን ያረጋግጣል። መልአኩ፥ እግዚአብሔር ስራውን የሚሰራበት intermediary ነው። በእርሱ አማካኝነት ይህን ሹመት ለሙሴ ሰጥቷል። በእርሱ አማካኝነት ስራውን ሊሰራ የቻለው ከእርሱ የተለየ አካል በመሆኑ ነው

በመጽሐፍ ቅዱስ፥ "በ" እርሱ አማካኝነት ሰራ ከተባለ፥ ያን አካል በመላክ ሊሰራ ያሰበውን ስራ ሰራ ማለት ነው። ያን ሌላ አካል ልኮ ያቀደውን ስራ ስለሚሰራ፥ "በእርሱ" ሰራ ይባላል። ለምሳሌ፦

"ጌዴዎንም እግዚአብሔርን። እንደ ተናገርህ የእስራኤልን ልጆች #በእኔ_እጅ ታድን እንደ ሆነ፥"
(መጽሐፈ መሳፍንት 6:36)

በዚህ ስፍራ፥ ጌዴዎን እግዚአብሔርን እንደተናገረው እስራኤልን በእርሱ እንጅ ያድን እንደሆነ ሲጠይቅ እንመለከታለን። ይህ ማለት፥ በእርሱ አማካኝነት እስራኤልን ያድን እንደሆነ እየጠየቀው ነው። እግዚአብሔር እርሱን ተጠቅሞ እስራኤልን እንደሚያድን ተናግሯልና። ይህ ማለት፥ እርሱን ልኮ እስራኤልን ያድናል ማለት ነው

" እግዚአብሔርም ወደ እርሱ ዘወር ብሎ። በዚህ በጕልበትህ ሂድ፥ እስራኤልንም ከምድያም እጅ #አድን፤ እነሆ፥ #ልኬሃለሁ አለው።"
(መጽሐፈ መሳፍንት 6:14)

ስለዚህ በእርሱ አማካኝነት ያድናል ማለት፥ እርሱን ልኮ ያድናል ማለት ነው። እርሱን በመላክ ሊፈጽም ያሰበውን ተግባር ይፈጽማል ማለት ነው። ይህ "በ" እርሱ አማካኝነት ሰራ ሲባል፥ ላኪና ተላኪ የሆኑ አካላት እንዳሉ የሚያረጋግጥ ነው። የላከውና የተላከው አንድ አካል ሊሆኑ አይችሉምና። ሌላ ምሳሌ፦

" #በሙሴና በአሮን #እጅ ሕዝብህን እንደ በጎች መራሃቸው።"
(መዝሙረ ዳዊት 77:20)

በዚህ ስፍራ፥ ንጉስ ዳዊት እግዚአብሔር ከግብፅ የወጣውን ሕዝቡን በሙሴና በአሮን እጅ እንደመራ ይናገራል። ይህ ማለት፥ እግዚአብሔር አሮንና ሙሴን ልኮ በእነርሱ አማካኝነት ሕዝቡን መራ ማለት ነው። እነርሱን በመላክ ሊፈጽመው ያቀደውን ተግባር አደረገ። አላማውንም በእነርሱ አማካኝነት ፈጸመ። ልኳቸዋልና። ይህ "በ" እርሱ ሰራ ሲባል ላኪና ተላኪ እንዳለ የሚያመለክት ነው። ላኪና ተላኪ ደግሞ አንድ አካል ሊሆኑ ስለማይችሉ፥ "በ" እርሱ ሰራ መባሉ የማንነት ልዩነት እንዳለ ያረጋግጣል

"ከግብጽ ምድር አውጥቼሃለሁ፥ ከባርነት ቤትም ተቤዥቼሃለሁ፤ በፊትህም #ሙሴንና #አሮንን ማርያምንም #ልኬልህ ነበር።"
(ትንቢተ ሚክያስ 6:4)

ስለዚህ እግዚአብሔር በመልአኩ አማካኝነት ሙሴን ገዢና ታዳኒ ማድረጉ፥ እግዚአብሔርና መልአኩ የተለያዩ አካላት መሆናቸውን ያረጋግጣል

በሚቃጠለው ቁጥቋጦ እግዚአብሔር መልአኩን ወደ ሙሴ ላከ፥ እርሱም በእሳት አምሳል ተገለጠለት። ከዚያም በላከው መልአክ አማካኝነት ገዢና ታዳጊ አድርጎ ሾመው። በመልአኩ አማካኝነት እግዚአብሔር ስራውንና እቅዱን ፈጸመ። መልአኩን ይህን ተግባር እንዲያደርግ (ሙሴን እንዲሾመው) ላከው። ይህ እግዚአብሔርና መልአኩ የተለያዩ አካላት መሆናቸውን ያረጋግጣል።

ይህ እስጢፋኖስ፥ መልአኩ ራሱ ክርስቶስ መሆኑን ለመመስከሩ ተጨባጭ ማስረጃ ነው።

ምክንያቱም ከላይ እንዳየነው፥ በተመሳሳይ አውድ የክርስቶስንም የመልአኩንም መለኮትነት መስክሯል። አሁን ደግሞ፥ በዚያው በራሱ አውድ፥ መልአኩ ልክ እንደ ክርስቶስ ከእግዚአብሔር የተለየ አካል መሆኑን እየመሰከረ ነው። ልክ ክርስቶስ ከአብ የተለየ መለኮታዊ አካል መሆኑን እንደመሰከረው ሁሉ፥ መልአኩም ከአብ የተለየ መለኮታዊ አካል መሆኑን መስክሯል። ይህ በማያሻማ ሁኔታ መልአኩ ራሱ ክርስቶስ መሆኑን ያሳያል።

በዚያው በራሱ አውድ፥ መልአኩ ልክ እንደ ክርስቶስ ሁለተኛ መለኮታዊ አካል መሆኑን መመስከሩ፥ ያ ለሙሴ የተገለጠው መልአክ ራሱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ያረጋግጣል። ምክንያቱም፥ በዙሪያው ባለው አውዱ ሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ሌላ ሁለተኛ መለኮታዊ አካል የለምና። የክርስቶስንም የመልአኩንም አምላክነት ከመሰከረ በኋላ፥ መልአኩ ልክ እንደ ኢየሱስ ሁለተኛ መለኮታዊ አካል መሆኑን የመሰከረበት ምክንያት ይህ ነው። መልአኩ ራሱ ጌታ ኢየሱስ ነውና

እግዚአብሔር ሙሴን በልጁ/መልአኩ በኩል የሾመው፥ በእርሱ አማካኝነት ስራውን ስለሚሰራ ነው።

መጽሐፍ ቅዱሳችን እንደሚያስተምረን፥ እግዚአብሔር ሊፈጽመው ያሰበውን ነገር በልጁ አማካኝነት ይሰራል።

ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን #በፈጠረበት #በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤
(ወደ ዕብራውያን 1:2)

በዚህ ስፍራ፥ እግዚአብሔር አለማትን የፈጠረው በልጁ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። ይህ ማለት ይህን ተግባር (አለምን መፍጠር) አብ የሰራው በልጁ አማካኝነት ነው ማለት ነው። ይህ እግዚአብሔር በልጁ አማካኝነት ስራውን እንደሚሰራ ያሳያል።

እግዚአብሔር #በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር #ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።
(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5:19)

በዚሁም ስፍራ እንዲሁ እግዚአብሔር አለሙን በክርስቶስ እንደታረቀ ይናገራል። ይህ ማለት እግዚአብሔር ልጁን ወደ ምድር በመላክ (1ዮሐ 4:10) አለምን ከራሱ ጋር አስታረቀ። የመታረቁን ስራ የሰራው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ነው። ይህ አብ ያቀደውን ነገር በልጁ አማካኝነት እንደሚሰራ ያረጋግጣል

ስለዚህ ሙሴንም ገዢና ታዳጊ አድርጎ የሾመው በዚሁ አኳሃን ነው። ልጁን/መልአኩን በመላክ ነው። በእርሱ አማካኝነት ገዢና ታዳጊ አድርጎ ሾመው። መለኮት የሆነውን ልጁን ልኮ ቤዛና ዳኛ አድርጎ ሾመው

በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር በተደጋጋሚ በልጁ/መልአኩ አማካኝነት ስራውን ሰርቷል። በእርሱ የይሁዳን ሕዝብ ከአሦራዊያን አድኗል (2 ዜና 32:21-22 ሆሴ 1:7) በእርሱ ኢየሩሳሌምን ሊያጠፋ ነበር (1 ዜና 21:15) ይህ እግዚአብሔር ስራውን በልጁ/መልአኩ እንደሚሰራ ያረጋግጣል። ስለዚህ፥ ሙሴንም ገዢና ታዳጊ አድርጎ የሾመው በዚህ አኳሃን ነው። በልጁ/መልአኩ አማካኝነት

እስጢፋኖስ መልአኩ ልክ እንደ ክርስቶስ፥ ከአብ የተለየ መለኮታዊ አካል መሆኑን መመስከሩ፥ ያ ለሙሴ የተገለጠው መልአክ ራሱ ልጁ ኢየሱስ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው። ይህም ክርስቶስ/መልአክ በአባቱ ተልኮ ሙሴን ገዢና ታዳጊ አድርጎ የሾመው ጌታ ነው።

ሌላው ሊስተዋል የሚገባው ነገር፥ እስጢፋኖስ በሚሞትበት ሰአት ስለ ክርስቶስ የተናገረው ነገር ነው።

እስጢፋኖስ በሚሞትበት ሰአት፥ ክርስቶስ የወጋሪዎቹን ኀጢአት እንዳይቆጥር ሲማጸነው አይተናል። እስጢፋኖስ በሰማይ ያለውን ክርስቶስን ኀጢአታቸውን አትቁጠር ብሎ ሊለምን የቻለው፥ ክርስቶስ በኀጢአት ጉዳይ ላይ ስልጣን ያለው አምላክ በመሆኑ ነው።

ተንበርክኮም። ጌታ ሆይ፥ ይህን #ኃጢአት #አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር።
(የሐዋርያት ሥራ 7:60)

ክርስቶስ ኀጢአትን የመቁጠርና ያለመቁጠር ስልጣን ያለው ኀጢአትን የመማር ስልጣን ስላለው ነው። ኀጢአትን የመማርና የመቁጠር ስልጣን ስላለው በሰማይ ሆኖ ይህ ሊባልለት ቻለ። በኀጢአት ጉዳይ ላይ መለኮታዊ ስልጣን አለውና

ከአብ የተለየ ማንነት የሆነው ክርስቶስ፥ በኀጢአት ጉዳይ ላይ ባለስልጣን መሆኑ በብሉይ ኪዳን ይገለጥ የነበረው የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው

ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱሳችንን ስናጠና ከአብ የተለየ ማንነት ሆኖ ሳለ፥ በኀጢአት ጉዳይ ላይ ባለስልጣን የሆነው የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን እንረዳለን፦
157 viewsedited  08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ