Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ መረጃ

የቴሌግራም ቻናል አርማ adissemereja — አዲስ መረጃ
የቴሌግራም ቻናል አርማ adissemereja — አዲስ መረጃ
የሰርጥ አድራሻ: @adissemereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.61K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎች በትኩሱ ና ሳይዉሉ እንዲሁም ሳያድሩ በቻናሉ በኩል ይደርሳሉ
ለአስተያየት እና ለማስታወቂያ ስራዎች 👇👇

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-04-10 19:21:00
በአማራ ክልል አጣዬ ከተማ፤ “በከባድ መሳሪያ የታገዘ” የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ መሆኑን ነዋሪዎች ገለጹ

በአማራ ክልል፤ ሰሜን ሸዋ ዞን፤ አጣዬ ከተማ ዛሬ ከንጋት ጀምሮ የተከፈተው በከባድ መሳሪያ የታገዘ ተኩስ እስከ አመሻሽ ድረስ መቀጠሉን ስድስት የከተማዋ ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ በከተማዋ ተኩስ እንዳለ ቢያረጋግጡም፤ በየትኛው አካል የተፈጸመ እንደሆነ እስካሁን አለመታወቁን ገልጸዋል።

የኤፍራታና ግድም ወረዳ ዋና ከተማ በሆነችው አጣዬ ከተማ ተኩስ የተከፈተው፤ ዛሬ ሰኞ ሚያዝያ 2፤ 2015 ከንጋቱ 12 ሰዓት ገደማ ጀምሮ መሆኑን የከተማይቱ ነዋሪዎች ተናግረዋል። የመጀመሪያው የተኩስ ድምጽ የተሰማው “አላላ” በተባለው የኤፍራታና ግድም ወረዳ ቀበሌ አካባቢ እንደሆነ ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።

የአጣዬ ከተማ ነዋሪዎች “በዲሽቃ እና ሌሎች ከባድ መሳሪያዎች የታገዘ” ሲሉ የጠሩት ተኩስ የተከፈተው፤ የከተማዋን ዙሪያ ከከበቡት ተራሮች ላይ “በሁሉም አቅጣጫ ነው” ይላሉ። የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አሳልፍ ደርቤ፤ “አጣዬ ዙሪያውን ጦርነት አለ” ሲሉ ተኩሱ በሁሉም አቅጣጫ የሚሰማ መሆኑን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል።
834 viewsedited  16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 13:34:09
ደቡብ ወሎ ሀይቅ
ተቀላቅላለች
1.2K viewsedited  10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 13:33:38 በጎንደር ከተማ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስን ጨምሮ የተለያዩ ክልከላዎች ተጣሉ!

የጎንደር ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ኮማንድ ፖስት የከተማዉን ሰላምና የሕግ የበላይነት ለማረጋገጥ እንዲቻል በቀን 1/8/2015 ተሰብስቦ የሚከተሉትን ክልከላዎች ማስቀመጡን አስታውቋል።

በዚህም መሠረት፦

1. በከተማው ያሉ ማንኛውም መጠጥ ቤቶችና ጭፈራ ቤቶች እስከ ምሽቱ 3:00 ሰዓት ዉጭ አገልግሎት መስጠት የተከለከለ ነው፤

2. በከተማው የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባለ 3 እግር ባጃጆች ከንጋቱ 12:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2:00 ሰዓት ዉጭ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው፤

3. ከተፈቀደለት የመንግሥት የፀጥታ ኃይል ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

4. ድምፅ አልባ መሳሪያዎችን ስለታማ የሆኑ እንደ ጩቤ፣ ገጀራ፣ አንካሴ፣ ጦርና ፌሮ ብረት ወዘተ የመሳሰሉትን ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

5. በሕግ የሚፈለጉ ወይም ተጠርጣሪዎችን ሽፋን የሰጠ፣ የደበቀ፣ የሀሰተኛ መረጃ ሰጥቶ ያሰመለጠ፣ የፀጥታ ሀይሎችን የሕግ ማስከበር ተልዕኮ ማደናቀፍ ማወክ በሕግ የተከለከለ ነው።

6. በማንኛውም ቦታና ሰዓት ጥይትም ሆነ ሮኬት ርችት መተኮስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

7. በተከለከሉ ቦታዎች በእምነት ተቋማት፣ በገቢያዎች፣ ሕዝብ በብዛት በሚሰበሰብባቸው ቦታዎች፣ በሆቴሎች፣ መጠጥ ቤቶችና ግሮሰሪዎች፣ ልዩ ልዩ መዝናኛ ቦታዎች ጦር መሳሪያ ይዞ መገኘትና መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

8. የሠራዊቱን ሚሊተሪ (አልባሳት) ከሰራዊቱ አባላት ውጭ መልበስ የተከለከለ ነው፦
        -የልዩ ኋይል ፣
        -የፓሊስ ፣
        -የመከላከያ ሠራዊት ፣
        -የፌዴራል ፓሊስ መልበስ የተከለከለ ነው።

9. ያልተፈቀደ ስብሰባዎችን ማለትም ያለ መንግስት እውቅና ውጭ ስብሰባ ማድረግ፣ ወታደራዊ ስልጠና መስጠት የተከለከለ ነው።

10. አድማ መቀስቀስ፣ ማድረግና ማስተባበር እንዲሁም መደበኛ ሥራን ማስተጓጎል በጥብቅ የተከለከለ ነው።

11. የአማራን ሕዝብ ከጥቃትና ከውርደት ለመታደግ መስዋትነት የከፈላችሁ  የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች፣ የአማራ ልዩ ኃይል አባላት በተፈጠረው የመረጃ ክፍተት ከተለያየ አካባቢ ተነስታችሁ ወደ ከተማችን የመጣችሁ በከተማችን በተዘጋጀው ማረፊያዎች እንድትሰባሰቡ እያሳሰብን ከዚህ ውጭ በተናጠልም ሆነ በቡድን መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ እና ጥይት መተኮስ የተከለከለ ነው

12. ፀጉረ ልዉጥ/አጠራጣሪ ሰው ከቤቱ ያሳደረ፣ ያከራየ፣ በሆቴሉ አልጋ ያስያዙ  እንዲሁም ለሚመለከተዉ የፀጥታ አካል ጥቆማ ያልሰጠ በሕግ የሚጠይቅ እንደሚሆን ተገልጿል።
1.2K viewsedited  10:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 14:25:28
#Update

የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ዶክተር ይልቃል ከፋለ ፤ የአማራ ልዩ ኃይልን በተለየ መንገድ ትጥቅ ለማስፈታት እና ለመበተን የተወሰነ ውሳኔ የለም አሉ።

ይህን ያሉት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ነው።

ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ምን አሉ ?

- በሀገር ደረጃ በሁሉም ክልሎች የሚገኙ ልዩ ኃይሎችን በፌዴራል የፀጥታ ተቋማት ለማደራጀት ተወስኖ ወደ ትግበራ ተገብቷል።

- ውሳኔው በፌዴራል መንግሥት እና በክልል መንግሥታት ስምምነት የተወሰነ ሲሆን በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ ይደረጋል።

- በአማራ ክልል ውሳኔውን ለመተግበር እየተሠራ ነው። ይህንን በተመለከተ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር ተወይይተናል።

- በአፈጻጸም ላይ በታየ ክፍተት እና በተነዛው ፕሮፖጋንዳ ችግሮች ተከስተዋል። ችግር እንኳን ቢኖር ተወያይቶ መፍታት ይቻላል።

- አብዛኛው የልዩ ኃይል አባል ውይይቱን አጠናቆ ውሳኔውን በካምፕ ሆኖ እየተጠባበቀ ነው።

- ልዩ ኃይሉ ትጥቅ የሚፈታና የሚበተን አይደለም ፤ በላቀ አደረጃጃት ኃላፊነቱን እንዲወጣ የሚያስችል ነው።

- ልዩ ኃይሉ ዓላማውን ተገንዝቦ ለበለጠ ተልእኮ ሊዘጋጅ ይገባል።

- የአማራ ሕዝብ በሁኔታው #ቅሬታ ውስጥ ገብቷል።ቅሬታው የመነጨው በተሟላ መንገድ ለሕዝቡ መረጃ ባለመድረሱ ነው።

- አደረጃጀቱ የሚደገፍ፣ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው የሀገርን አንድነት የሚያረጋግጥ ነው።

- አደረጃጀቱ የአማራን ክልል በተለየ መንገድ የሚጎዳ አይደለም።

- የአማራ ክልልን ልዩ ኃይል በተለየ መንገድ ትጥቅ ለማስፈታት እና ለመበተን የታለመ ዓላማ የለም።

- በተፈጠረ የመረጃ ክፍተት በአንዳንድ ከተሞች የሰላማዊ ሰልፍ እንቅስቃሴ፣ የአድማ ጥሪ እና የሰዎች እና የተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴን የመገደብ አዝማሚያዎች እያታዩ ናቸው። አላስፈላጊ አካሄዶች አውዳሚ እና አክሳሪ እንጂ አትራፊ አይደሉም።

- የአማራ ክልል በጦርነት የከረመ ክልል ነው ፤ በጦርነቱ ምክንያት ሕዝቡ ተጎሳቁሏል፣ በጦርነቱ ምክንያት የተጎዳው ኅብረተሰብ እና መሠረተ ልማት ገና ማገገም አልቻለም ፤ ከአንደኛው ችግር ሳናገግም ወደ ሌላ ችግር መሸጋገር ሕዝቡን መጉዳት ነው።

- በመወያየት አላስፈላጊ ጉዳዮችን ማስቆም ይቻላል ፤ ሁሉም አውዳሚ የሆነውን ጉዳይ መከላከል ይገባዋል።

- ግጭት እንዳይፈጠር ወጣቶች እና የሃይማኖት አባቶች የሚመሰገን ሥራ እየሠሩ ናቸው።

- የአማራ ክልል ሕዝብ ጉዳዩን በውል በማጤን፣ በመመካከር እና ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት አስቀድሞ በማሰብ ማስከን ይገባል።

- የአማራ ልዩ ኃይል በተለየ መንገድ የሚጎዳ ውሳኔ አልተወሰነም፣ ወጥና ሀገራዊ ውሳኔ ነው የተደረገው፣ በሁሉም ክልል የሚፈጸም ነው፣ ውሳኔው ለሀገር ግንባታ ታላቅ አስተዋጽዖ አለው።

- ከወቅታዊ ጉዳይ አንጻር የሚነሳው ጥያቄ ትክክል ቢሆንም አፈጻጸሙ ለሀገር የሚጠቅም መሆኑን መገንዘብ ይገባል።

- ከካምፕ የወጡ የልዩ ኃይል አባላት እንዲመለሱ ማድረግ ይገባል።

- የአማራ ሕዝብ ጉዳዩን በሰከነ መንገድ ማየት አለበት ፤ ችግሩ ዳር ወጥቶ ግጭት እንዳይከሰት እያደረጉ ላሉ አካላት ምስጋና ይገባል።

- የልዩ ኃይል አባላት ትጥቅ አትፈቱም፣ የምትበተኑበት ነገር የለም፣ ወደ ላቀ ተልእኮ ነው የምትሸጋገሩት።

- በመደማመጥ ችግሮቻችን እንፈታለን፣ የአማራን ጥያቄዎች እናስመልሳለን።

#AMC

@tikvahethiopia
357 views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 14:25:27
" ሳይገባቸው የሚቃወሙትን ለማስረዳትና ለማሳመን ጥረት እናደርጋለን። ሆን ብለው የአፍራሽነት ሚና በሚጫወቱት ላይ ደግሞ ተገቢው የሕግ ማስከበር እርምጃ እንወስዳለን " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከዚህ በኋላ ክልሎች የፖሊስ ኃይላቸውን አጠናክረው ወንጀልን በመከላከልና አካባቢያዊ ጸጥታን በማስከበር ላይ ብቻ ያተኩራሉ አሉ።

ይህን ያሉት ዛሬ የልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀትን በተመለከተ ባወጡት መግለጫ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ ከአሁን በኃላ ክልሎች የፖሊስ ኃይላቸውን አጠናክረው ወንጀልን በመከላከልና አካባቢያዊ ጸጥታን በማስከበር ላይ ያተኩራሉ ፤ ከየትኛውም ኃይል የሚሰነዘር፣ የሀገርን ድንበር ህልውናና ሉዓላዊነት የሚዳፈር ኃይል ሲነሣ ደግሞ የመከላከያ ሠራዊቱ እርምጃ ይወስዳል ብለዋል።

ለዚህ የሚሆን አደረጃጀትም በተግባር ላይ ውሏል ሲሉ አሳውቀዋል።

" የክልሎች ፉክክርና ትብብር በልዩ ኃይል ግንባታ ሳይሆን በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ ልማትና በዴሞክራሲያዊ ባህል ላይ ይሆናል " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " ይህ ውሳኔም ለኢትዮጵያ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትና ለሕዝቡ ሰላም ሲባል ዋጋ ተከፍሎም ቢሆን ተግባራዊ ይደረጋል። " ብለዋል።

" ሳይገባቸው የሚቃወሙትን ለማስረዳትና ለማሳመን ጥረት እናደርጋለን። " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ሆን ብለው የአፍራሽነት ሚና በሚጫወቱት ላይ ደግሞ ተገቢው የሕግ ማስከበር እርምጃ ይወሰዳል። ለዚህም በቂ ዝግጅት ተደርጓል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

የሚመለከታቸው ተቋማትና ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በአጠቃላይ ፤ የውሳኔውን ሃገራዊ ፋይዳና የሚያስገኘውን ዘላቂ ጥቅም ከግምት በማስገባት ለተግባራዊነቱ ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

(ሙሉ መግለጫቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
323 views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 14:25:27
#Update

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ (አብን) ዛሬ እሁድ ባወጣው መግለጫ መንግሥት ከልዩ ኃይል ጋር በተያያዘ ያሳለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ በመግፋቱ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ከፍተኛ ህዝባዊ ቁጣ መቀስቀሱን ገልጿል።

ፓርቲው እስካሁን ድረስ ለሀገራዊ አንድነት እና ሰላም ሲባል ጉዳዩን በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ሲከታተል መቆየቱን ገልጾ ይሁንና መንግስት ችግሩን በሰከነ መንገድ ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ ከዕለት ወደ ዕለት የለየለት የኃይል ፣ የአፈና እና የማደናገር አማራጭ እየገባ መሆኑን መረዳቱን አመልክቷል።

" መንግስት ችግሩን በሰከነ መንገድ ፣ በውይይት ፣ በጋራ መግባባት እና በመተማመን የመፍታት ኃላፊነት ያለበት ቢሆንም በስህተት ላይ ሌላ ስህተት እየደረበ እና ችግሩን በአፈና እና በጉልበት ለመፍታት ቆርጦ የተነሳ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ከዛሬ ጀምሮ ለችግሩ ዘላቂ እልባት እስከሚሰጥ ድረስ መንግስት እና ግብረ-አበሮቹ በአማራ ልዩ ኃይል ፣ በፋኖ እና በአጠቃላይ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚነዟቸውን የሀሰት ፕሮፖጋንዳዎች በይፋና በተከታታይ አጋልጣለሁ " ብሏል።

አብን በመግለጫው የአማራ ልዩ ኃይልን ለማፍረስ እና ትጥቅ ለማስፈታት መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ እና የሚያደርገው እንቅስቃሴ ኃላፊነት የጎደለውና ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ድጋሜ አሳውቋል።

የብልፅግና ፖርቲ ሥራ አስፈፃሚ ያሰፈው ውቃኔ መሬት ላይ ያለውን ሃቅ ያላገናዘበ ፣ መርኅ አልባ ፣ አድሏዊ እና አምባገነናዊ ነው ሲል ገልጾታል።

ውሳኔውና የአፈፃፀም ሂደቱ በሕግ አግባብ የተመራ ፣ መርኅ ተኮር እንደሆነ ፣ ውይይት እንደተደረገበት እና መግባባት የተደረሰበት እንደሆነ ለማስመሰል የሚቀርቡ አስተያየቶችም በአጠቃላይ ሃሰት ናቸው ብሏል።

(የአብን ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
293 viewsedited  11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 14:25:26
#Update

በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መንግስት ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት የጀመረውን ተግባር የሚቃወሙ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ዛሬም መቀጠላቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ዛሬ በጎንደር ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ የተደረገ ሲሆን የሰልፉ ተካፋዮች " የአማራ ልዩ ኃይል ለአማራ ህዝብ የጀርባ አጥንት ነው ፤ " የእርስቶቻችን ጉዳይ ለአፍታ የምንረሳው አይደለም " የሚሉና ሌሎችም መልዕክቶችን በማስተላለፍ የመንግሥትን ተግባር ተቃውመዋል።

በላሊበላ ከተማ በተመሳሳይ " የአማራ ልዩ ኃይል የጀርባ አጥንታችን ነው፤ ከልዩ ኃይል ላይ እጃችሁን አንሱ " በሚል የመንግሥትን ውሳኔ የሚቃወሙ መልዕክቶች የተላለፉበት ሰልፍ መደረጉ ተሰምቷል።

ፎቶ ፦ ከማህበራዊ ሚዲያዎች
262 viewsedited  11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 14:25:26
#Update

የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ፤ የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ የማደራጀት ሥራ ለሕዝብ አገልግሎት መስዋዕትነት ሲከፍሉ የነበሩ የልዩ ኃይል አባላትን ለተጨማሪ ተልእኮ ከማዘጋጀት ያለፈ ዓላማ የለውም ሲሉ ተናገሩ።

ይህንን ያሉት ክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት እየተከናወነ የሚገኘውን ሥራ አስመልክቶ የፌደራልና የክልል የጸጥታ ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ውይይት ካደረጉ በኃላ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ማብራሪያ ነው።

አቶ ደሳለኝ ጣሰው ፤ የልዩ ኃይል አባላትን መልሶ ማደራጀቱ ለተጨማሪ ተልዕኮ ከማዘጋጀት ያለፈ ዓላማ የለምው ያሉ ሲሆን " ልዩ ኃይሉን መልሶ የማደራጀት ሥራው መጠራጠርን በማስቀረት ዜጎች የሚተማመኑበትን ኀይል ለመገንባት ያግዛል " ብለዋል።

የልዩ ኃይል አባላቱ እንደ የሙያቸው ሥልጠና እንደሚወስዱ ከዚያም ፍላጎታቸውን መሰረት በማድረግ ወደ ተለያዩ የጸጥታ ዘርፍ መዋቅሮች ውስጥ እንደሚገቡ አመልክተዋል።

በፌደራልና የክልል የጸጥታ ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ውይይት ላይ የክልል ልዩ ኃይሎች ላይ እየተደረገ ያለው የመልሶ ማደራጀት ሥራ " ለተወለድኩበት ብሔር ነው የቆምኩት የሚለውን እሳቤ በማስተካከል " ኢትዮጵያውያን በእኩል የሚተማመኑበት የጸጥታ አካል ለመፍጠር ይረዳል ተብሏል።

" ልዩ ኀይሉ ሊበተን ነው ፤ ሊፈርስ ነው፤ ትጥቅ ሊፈታ ነው " በሚል የሚነዛው አሉባልታ ትክክል እንዳልሆነ ተነግሯል።

መንግሥት የልዩ ኃይል አባላትን መልሶ የማደራጀት እንቅስቃሴ ውስጥ እንደሚገኝ እየገለፀ ባለበት በዚህ ወቅት በተለይ በአማራ ክልል አካባቢዎች ሂደቱን የሚቃወሙ ነዋሪዎች መንገድ በመዝጋት፣ እንቅስቃሴ በማቆም እየተቃወሙ ይገኛሉ።

ተቃውሞው የአማራ ህዝብ የደህንነት ስጋት ባልተቀረፈበት ሁኔታ ትጥቅ ለማስፈታት የተጀመረ እንቅስቃሴ ነው ፣ ህወሓት ትጥቁን ሙሉ በሙሉ ባልፈታበት ሁኔታ የሚፈፀም ነው ፣ ይበልጥ የአማራ ክልልን ህዝብን ለጥቃት በሚያጋልጥ ሁኔታ እየተደረገ ያለ ነው ፤ ከዚህ አልፈ ሲል ሂደቱ ለምን አማራ ክልል ላይ በድብቅ እንዲጀመር ተደረገ በሚል እንደሆነ ለመስማት ተችሏል።

የፌዴራል መንግሥት ከቀናት ለፊት በሰጠው መግለጫ በሁሉም ክልል በተመሳሳይ ወቅት የልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ስራ እንደጀመረ ፣ ትጥቅ መፍታ የሚባል ነገር ከዚህ ጋር እንደማይገናኝ ሂደቱ ላይ እንቅፋት ለመሆን እየሞከሩ ያሉት ሀሰተኛ መረጃ ለህብረተሰቡ እያሰራጩ ያሉ አካላት ስለመሆናቸው ገልጿል።

@tikvahethiopia
281 views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 11:13:21
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችንና ትምህርት ቤቶች ትምህርት ለማስጀመር ሁሉን አቀፍ ዝግጅት እየተደረገ ነው

በትግራይ ክልል የሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎችን እና አጠቃላይ መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር የስርዓተ ትምህርትና የመምህራን ዝግጅት እየተደረገ ነው።

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች፣ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶችና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች በክልሉ ትምህርት ማስጀመር የሚያስችል ውይይት አድርገዋል።

መንግስትና ህወሃት በፕሪቶሪያ የደረሱትን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍ ከማቅረብ ጀምሮ የክልሉን ህዝብ በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችሉ የመልሶ ግንባታና መሰረታዊ አገልግሎቶች እየተሰጡ ነው።

መንግስት በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም፣ የታጠቁ ኃይሎች ትጥቅ ፈትተው ወደ መደበኛ ህይወት እንዲመለሱ፣ መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ፣ እንዲሁም ትምህርት እንዲጀመር የሰላም ስምምነቱን እየተገበረ ነው።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ በውይይቱ ላይ እንዳሉት፣ በግጭቱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የዩኒቨርሲቲዎችና አጠቃላይ መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ ነው።

በዚህም የትምህርት ተቋማት የደረሰባቸውን የጉዳት መጠን በማጥናት ትምህርት ለመጀመር የሚያስፈልጉ ጉዳዮችን ለይተን ቅድመ ዝግጅት ጀምረናል ብለዋል።
605 viewsedited  08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 10:13:01 ጠ/ ሚ ዐብይ አህመድ ልዩ ሀይልን በሚመለከት ምን አሉ?


*የልዩ ኃይል አባላትን ወደ መከላከያ ወይም ወደ ፖሊስ እንዲገቡ የማድረግ አጀንዳ ለረጅም ጊዜ ሲታሰብበትና ሲመከርበት የቆየ ጉዳይ ነው።

* ጉዳዩ እንዲነሣ ያደረጉት ሁለት ምክንያቶች ናቸው። አንዱ የልዩ ኃይል አባላትን ጥቅማ ጥቅም፣ ዕድገትና ማዕረግ የተመለከተ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ አደረጃጀቱን ምክንያት በማድረግ በተደጋጋሚ ያጋጠሙንን ፈተናዎች የተመለከተ ነው።

* በሀገር ውስጥና በውጭ የሚሰጡ ወታደራዊ ትምህርቶችንና ሥልጠናዎች ሊደርሷቸው ያስፈልጋል። የላቁ ወታደራዊ መሣሪያዎችን ሊታጠቁ ይገባል። ከፍ ያሉትን ወታደራዊ ማዕረጎች በቆይታቸውና በጀብዷቸው ሊቀዳጁ ይገባል።

*ይህ መሆን የሚችለው ደግሞ ወደ መደበኛ የጸጥታና ደህንነት ተቋማት ማለትም በሀገር መከላከያ ሠራዊት ውስጥ አልያም በፌደራል ፖሊስ ሠራዊት ውስጥ እና በክልሎች ፖሊስ ሠራዊት ውስጥ መካተት ሲችሉ ብቻ ነው።

*እነዚህን የመሰሉ በውጊያ የተፈተኑ ኃይሎች በጊዜያዊ የልዩ ኃይል አደረጃጀት ብቻ ወስኖ ማስቀረት ሀገርንም አባላቱንም መጉዳት ነው።


*ኢትዮጵያ ከክልል ልዩ ኃይሎች ጋር በተያያዘ ከአንዴም ሁለት ጊዜ የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት የተገዳደሩ ፈተናዎች ገጥመዋት እንደነበር አይዘነጋም። ከአንድነትና ሉአላዊነት ሥጋትነት በመለስም በክልሎች መካከል የማያስፈልግ ተፎካካሪነትና ተገዳዳሪነት እንዲፈጠር መንስኤ ሲሆኑ እናያለን።

* ከሕገ ወጥ የኬላ ዝርጋታ፣ ከኮንትሮባንድ፣ ከሽፍትነት፣ ወዘተ ጋር የተያያዙ ፈተናዎችም እየተስተዋሉ ናቸው። እነዚህ ችግሮች የመነጩት ለጊዜያዊ መፍትሄነት የፈጠርናቸውን አደረጃጀቶች እንደ ዘላቂ መፍትሄ መቁጠር በመጀመራችን ነው።

*የክልል ልዩ ኃይሎችን ጉዳይ በይደር ያቆየንበት ምክንያት ነበረን። አንደኛው የመከላከያ ኃይላችንን በበቂ መልኩ ለማደራጀት ጊዜና ዐቅም ስላስፈለገን ነበር። ሁለተኛው ደግሞ በወቅቱ በሀገራችን ላይ ከተጋረጠብን አደጋ አንጻር እነዚህን መሳይ ሥራዎች ለማከናወን የሚያስችል ሁኔታ ስላልተፈጠረ ነበር።

*ባለፉት ሦስት ዓመታትም ከሕዝብ ጋር በተደጋጋሚ በተደረጉ ውይይቶች  ልዩ ኃይሎች ወደ መከላከያ እንዲጠቃለሉ ሕዝቡ ጠይቋል። የልዩ ኃይል አባላትም ከሜካናያዝድ ሥልጠና፣ ከደመወዝ፣ ከማዕረግ ዕድገት፣ ከትምህርት ዕድሎችና ከሌሎችም ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ነገሩን በተደጋጋሚ አንሥተውታል።

*የልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች እንዲገቡ ለማድረግ ሲወሰን፣ ተገቢው ዝግጅት ተደርጎበት ነው።

*የልዩ ኃይል አመራሮችና አባላት እንዲወያዩበት ማድረግ፣ወደ ሌሎች ጸጥታ መዋቅሮች የማስገባቱ ተግባር በሁሉም የክልሎች ልዩ ኃይሎች ላይ እንዲተገበር፣ አባላቱ ወደ መከላከያ፣ ወደ ፌደራል ፖሊስ ወይም ወደ ክልል ፖሊስ እንዲገቡ፣ ጉዳዩ የትጥቅ መፍታት ጉዳይ ሳይሆን የበለጠ ሥልጠናና ትጥቅ አግኝተው ሀገርን በተሻለ ወደሚያገለግሉባቸው መዋቅሮች እንዲገቡ የሚያደርግ መሆኑንና ይሄንን ሥራ ለማደናቀፍ የሚነሡ አካላት እንደሚኖሩ፤ መጀመሪያ በመወያየትና በማሳመን፤ ከዚህ ያለፈ ተግባር የሚፈጽሙ ካሉም ሕግ የማስከበር ሥራ እንዲሠራ የሚሉ ናቸው።

*ዛሬም የየክልሉ ልዩ ኃይሎችን እስከ ዛሬ ለሰጡት አገልግሎት አመስግነን፣ ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የምናካትትበት ወቅት ላይ እንገኛለን። ይህ ውሳኔ በሁሉም ክልል አመራሮች በጋራ የተወሰነና በጋራ የሚተገበር ነው።
702 viewsedited  07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ