መስጠት አለብህ! የፈጣሪ የሒሳብ ቀመር ደስ የሚለው አንተ ስታካፍል እሱ አየደመረ እያባዛ መስጠቱ ነው። የተሰጠህን ስጦታ ለራስህ ብቻ ባስቀረኸው ቁጥር እንዳይጨምር እያረከው መሆኑን ሁሌም አስታውስ። ወዳጄ የምትሰጠው ገንዘብ ብቻ አይደለም፤ ለምትወዳቸው ጊዜህን ስጣቸው! ለተጨነቁ ጆሮህን ስጥና አድምጣቸው! ግራ ለገባቸው ሀሳብህን አካፍላቸው! ያኔ ባለህ ገንዘብ፣ ዕውቀትና ጥበብ ላይ ብዙ እጥፍ ሲጨመርልህ ታይና በግርምት እጅህን አፍህ ላይ ትጭናለህ። @ablat2 የእናንተው ምርጥ ጓደኛ! 69 views·٠•● sad ⓑⓐⓚⓘ ●•٠·, 19:52