Get Mystery Box with random crypto!

በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት በአሸናፊ ከበደ የክዋኔ ጥበባት ማዕከል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት በመታደሜ | Abiy Ahmed Ali 🇪🇹

በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት በአሸናፊ ከበደ የክዋኔ ጥበባት ማዕከል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት በመታደሜ ደስ ብሎኛል። አሸናፊ ከበደ ከያኒ ብቻ ሳይሆን የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት የመጀመሪያው ዳይሬክተር ነበር። የአዲሱ ማዕከል ዳይሬክተር ግርማ ይፍራሸዋ ደግሞ በቀደመው እና በአሁኑ የኢትዮጵያ ሙዚቃ መካከል ድልድይ በመሆን ያገለግላል። ይህን መሰል ድልድይነት እና ቀጣይነት በሁሉም ተቋሞቻችን አስፈላጊ ነው። ሙዚቃ ኃይል አለው። ይህን ኃይል ለወጣቶቻችን አብርሆት ልንጠቀምበት ይገባል። ጥበባት መጪውን ትውልድ ቅርጽ በማስያዝ እና የከተማችንን የቱሪዝም መስሕብ በማላቅ ከፍ ያለ ሚና ይጫወታሉ። ይህን ዐቅም በምሉዕነት መጠቀም ይገባናል።

I am pleased to witness the inauguration of the Ashenafi Kebede Performing Arts Center at the Yared School of Music. Ashenafi Kebede was not only an artist but also the first director of the Yared Music School. The new center’s director, Girma Yifrashewa, serves as a bridge between the past and the future of music in Ethiopia. Such continuity and linkage are essential in all our institutions. Music is powerful, and we must use this power to enlighten our youth. The arts play a vital role in shaping future generations and enhancing our city’s capacity to attract tourism. We must fully utilize this potential.