ለሰዎች መናገርና ሰዎችን መምራት ከመጀመራችን ቀድመን ወይም ብያንስ ከፊል ግዜ ወስደን ራስን በማስለም እርካብ ወደ ላይ ማውጣት አለብን።
በተቀየረ እኛነታችን መጠን ነው ሌሎችን አስረግጠን መቀየር የምንችለው።
ራስን መቅረፅ፣ ራስን መስራት፣ ራስን ማለምለም፣ ራስን ማሰልጠን፣ ራስን ማብቃት፣ ራስን ማበልፀግ፣ ራስን ማነፅ፣ ራስን ማዳበር መቅደሙ የምናስተምረው ተግባራዊነት እንዲሆን ሙሉ አቅም ሲለሚሆነን ነው።
የኖርነውን ማስተማር ምሳሌ ለማቅረብም አያስቸግርም፣ እርግጠኛም ሆነን ሀሳባችንን እናስተላልፋለን።
የምንለውን ጉዳይ ክብደትና ቅለትም እንዲሁ መዝነን ማስተላለፍ ይቻለናል። ፋይዳ ያለውን ነጥብ እየለየን መምራት ይቀለናል።
ይህንን page Follow አድርጉ https://www.facebook.com/profile.php?id=100082999208494