Get Mystery Box with random crypto!

'ሰልፍ እና መፈክር ይቁም' 'ለምን በኦሮሚያ ብቻ ሰልፍ?' 'ንፁሀንን እየገደሉ እና ጦርነት ከ | ዘሪሁን ገሠሠ

"ሰልፍ እና መፈክር ይቁም"

"ለምን በኦሮሚያ ብቻ ሰልፍ?"

"ንፁሀንን እየገደሉ እና ጦርነት ከዚህም ከዚያም እያሞቁ "መከላከያን እንወዳለን" ማለት አይቻልም።" አቶ ታዬ ደንደኣ

<<እስቲ እንነጋገር እውነት የሀገር መከላከያን እንወዳለን....? አዎን እንወዳለን ሁሉም ወንድሞቻችን እና ልጆቻችን ናቸው። በሰላም ወተን መግባታችን በነሱ ነው እና ልንጠላቸው አንችልም እናከብራቸዋላን። ነገር ግን የሀገር መከላከያን ትክክለኛ ትርጉም ማወቅ እንጅ ሰልፍ እና የመፈክር ጋጋታ አያስፈልግም።

የእውነት መከላከያችንን የምንወድ ከሆነ ያለባቸውን ሸክም ልናቀል ይገባል። ይሄ ደሞ የሚሆነው እውነተኛ ሰላም እና እርቅ በመፍጠር የህዝብን ሰላም ስናረጋግጥ ነው። ከዛ በተረፈ ንፁሀንን እየገደሉ እና ጦርነት ከዚም ከዛም እያሞቁ "መከላከያን እንወዳለን" ማለት አይቻልም።

እውነት መከላከያን እንወዳለን ከሆነ ህዝብን በሰልፍ ማድከም አስፈላጊ አይደለም። ሰላም እና እርቅ በማውረድ ላይ እናተኩር። ከህወሃት ጋር ያደረግነውን ንግግር ከኦነግ ጋርም እናድርግ። የቤት ውስጥ ፀብ እናቁም ከጎረቤት ጋርም አንጋጭ። መከላከያ በቴክኖሎጂ እናዘምን የተጎዱትን እንካስ።

እናም እንዲህ እንላላን መከላከያ የመላው ህዝብ ሆኖ ሳለ በኦሮሚያ ብቻ ሰልፍ የሚደረገው ለምንድነው.??? እውነት እላቹሀለው ይህ ለኦሮሞ ህዝብም ለመከላከየውም ጥሩ አይደለም። ሰላም ሰላም ሰላም ለሀገራችን!>> //አቶ ታዬ ደንደአ //