Get Mystery Box with random crypto!

አቶ ብርሀኑ ጁላ ፥ ረዘም ባለው ጥላቻ ፥ እብሪት ፣ ማንአለብኝ ባይነት ፣ ፍረጃና ስድብ ብቻ በተ | ዘሪሁን ገሠሠ

አቶ ብርሀኑ ጁላ ፥ ረዘም ባለው ጥላቻ ፥ እብሪት ፣ ማንአለብኝ ባይነት ፣ ፍረጃና ስድብ ብቻ በተስተዋለበት የትናንቱ መግለጫቸው ፦

የአማራ ብልፅግናን << የተቀበሉና ያፈነገጡ >> ብለው ለሁለት ከፈሉ፡፡ ፋኖን <> ፅንፈኛና ፅንፈኛ ያልሆነ >> በማለት በተመሳሳይ በሁለት ጎራ መደቡ፡፡ ቀጠሉና " ልዩ ሀይሉ ለምን ተነካ !" ሲል ለክብሩ በይፋ ለትግል የተነሳውን ፋኖ ደግሞ << ፋኖ ልዩሀይሉን ጨፍጭፏል ፥ ዘርፏል …ወዘተርፈ >> ሲሉ በመፈረጅ ፤ አስነዋሪና ይሉኝታቢስነት በተንፀባረቀበት መልኩ ፦ የእርስበርስ መከፋፈልን ለመፍጠር ብሎም አንዱን በአንዱ ላይ ለማስነሳት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡

ታዲያ ይህን ሠው "ይሉኝታ ቢስ የሴራ ፖለቲከኛ" እንጂ የማዕረግ ስሙን አስቀድሞ "የኢትዮጵያ የጦር ሀይሎች ኤታማዦር ሹም " ብሎ መግለፅ ይቻላልን ?

በነገራችን ላይ ይሄ በነውር የተሞላው መግለጫ ፤ ቀጣዩን ሁኔታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ የጥላቻ ፖለቲካውን የወደፊት አቅጣጫ አመላካች እንጂ በቀላሉ የሚታለፍ ጉዳይ አይሆንም!