በዛሬው የሱዳን አየር ድብደባ ፥ የሳዑዲ ኤርባስ - A330-300 የመንገደኞች አውሮፕላን ተመትቷል!
ዛሬ በሱዳን ካርቱም አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተፈፀመው የአየር ጥቃት ከወደሙት አውሮፕላኖች መካከል የሳኡዲ አረቢያ Airbus A330-300 (HZ-AQ30) እና የዩክሬናውያኑ ስካይአፕ አየር መንገድ Boeing 737-800 (UR-SQH) ይገኙበታል፡፡
አውሮፕላናቹ የአየር ጥቃቱን ያስተናገዱት መንገደኞችን ለማሳፈር እየተዘጋጁ ባሉበት ሰአት ሲሆን ፥ ሳዑዲ ከጥቃቱ በኃላ መንገደኞቹን ካርቱም በሚገኘው ኤምባሲዋ ገብተው ከለላ እንዲያገኙ አድርጋለች፡፡
ወደሱዳን የሚደረጉ በረራዎች ሙሉ በሙሉ ተቋርጠዋል!