ሌላ ሌላውን እንተወውና...! የመከላከያ ሠራዊቱ መፈክር " የኢትዮጵያን ዳር ድንበርና ሉአላዊነት እናስከብራለን! " ቢልም ቅሉ ፦ ከሰሞኑ እንኳ የሱዳን ጦር ቀድሞ ከያዘው ወደ70 ኪ.ሜ የሚጠጋ የኢትዮጵያ ግዛት ዘልቆ በመግባት ፥ በመተማ ዮኋንስ ሰፈር - 4 የልማት ቦታን በመያዝ የወረራ ማስፋፋቱን ቀጥሏል! የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ከድንበራቸው ወደ 200 ኪሎ ሜትር ዘልቀው በመግባት የአካባቢዎቹን ስያሜ በመቀየር ፥ በስፍራው ያሉ ነገዶችን በመጨፍጨፍ ፤ የወርቅ ማዕድን ማውጫዎችን ጨምሮ በርካታ ኢኮኖሚያዊ ቱሩፋት የሚያስገኙ ግዛቶችን እንደተቆጣጠሩ ናቸው! በዘመነ-ደርግ የሱዳን ሰራዊት አይደለም ወረራ መፈፀም ወደኢትዮጵያ ድንበር ተጠግቶ እንኳ መሽናት አይችልም ነበር! ኧረ በዘመነ-ህወሓትም የሀገር ሉአላዊነትና ዳር ድንበር ጉዳይ ጥያቄ ምልክት ውስጥ አልገባም! 3.5K views13:38