ማንኛችንም አሸናፊና ተራፊ ወደማንሆንበት ፥ የእልቂት ውቅያኖስ እየተዘፈቅን ነው! ከስልጣኔ ማማ ላይ የተቆናጠጡት ጀርመኖች ያንን የፋሽስታዊ ስርአት የዘር ፍጅት " የምናፍርበት ታሪካችን!" ብለው በሙዚየም ለአለም መማሪያነት ያስጎበኛሉ፡፡ ዛሬ ላይ " ሁቱና ቱትሲ" ተባብለው ለመጠራራት ሁሉ የሚፈሩት ሩዋንዳውያን በቀናት ሚሊየኖችን ጭጭ ምጭጭ ያደረገውን አስከፊ ጭፍጨፋ " አይደለም እንደዚያ አይነቱ ጥቁር ታሪክ ሊደገምና ፥ የግለሰቦች ፀብ እንኳ መስማት አንሻም!" ሲሉ ከትናንት እልቂት ተምረው ፥ በጥሩ ሀገራዊ የእድገትና የሰላም መንገድ ላይ እየተጓዙ ይገኛሉ! እኛ ግን ላለፉት 5 አመታት ፍጅትና እልቂት እየተፈፀመ "በቃ!" ማለት ተስኖን ፥ ከሩዋንዳም ሆነ ከጀርመን ከፍ ባለ ደረጃ ፥ ወደፍጅት ውቅያኖስ መንደርደራችንን ቀጥለናል! ላለፉት 5 አመታት በአብዛኛው የተፈጀውና እየተጨፈጨፈ ብሎም እየተፈናቀለ ያለው የአማራ ህዝብ ብቻ ቢሆንም ፥ እመኑኝ! ይህ ጭካኔና "ነግ በእኔ" የማያስብል የዝምታ መንገዳችን ፥ ማንኛችንንም ወደማያስተርፍ የእልቂት አዘቅት እያንደረደረን ነው! "ልብ ያለው ፥ ልብ ይበል!" 3.9K viewsedited 14:12