#Tigray, #Mekelle የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት መቋጫ ያገኝ እና አስተማማኝ ሰላም ይሰፍን | Mereja News Live
#Tigray, #Mekelle
የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት መቋጫ ያገኝ እና አስተማማኝ ሰላም ይሰፍን ዘንድ ጥረት እያደረጉ የሚገኙት የአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞ ናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ትግራይ ክልል ይገኛሉ።
አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝደንት መቐለ እንደሚገኙ በመግለጽ ከዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ጋር እንደመከሩ ገልጸዋል።
ኦባሳንጆ እና ዶ/ር ደብረፅዮን በቀጠናዊ ጉዳዮች ጋር መምከራቸው የተነገረ ሲሆን ምክክሩን የተመለከተ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልሆነም።