Get Mystery Box with random crypto!

“የገና ስጦታ” ለየኔታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰባት የአዋጅ አጽዋማት አሏት | ዜና ገዳማት-ማኅበረ ቅዱሳን

“የገና ስጦታ” ለየኔታ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰባት የአዋጅ አጽዋማት አሏት። በዓመት የሚታከብራቸው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኝ ዐበይትና ዘጠኝ ንኡሳን በዓላትን ታከብራለች። በየወሩ የምታከብራቸው በዓላትም አሉ። አጽዋማቱም ሆነ በዓላቱ ትውፊታዊ መነሻ ሲኖሯቸው ከነገረ ድኅነት፣ ከመንፈሳዊ ሕይወት፣ ከሱታፌ ምሥጢራት እና ከሃይማኖታዊ ትሩፋት ጋር ግንኙነት አላቸው።
ነገር ግን አጽዋማቱንም ሆነ በዓላቱን ለመንፈሳዊ ዓላማ አጠቃቀማችን በቂ አለመሆኑን መረዳት ይገባል። በበዓላት አከባበራችን ላይ የሚታየውን ክፍተት በመሙላት ለድኅነትና መነሻ ለሆነው ዓላማ ከማዋል አንጻር ማኅበረ ቅዱሳን ጾመ ነቢያትን በሙሉ እስከ ልደት ድረስ የሚቆይ “የገና ስጦታ ለየኔታ” በሚል መሪ ቃል የገቢ ማሰባበሰቢያና የስጦታ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል። በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ ኅዳር 25/2014 ዓ.ም ጠቅላይ ቤተ ክህነት ከ7፡30 ጀምሮ በመገኘት በጦርነቱ ጉዳት የደረሳበቸውን ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች እንጠናክር፡፡