Get Mystery Box with random crypto!

በሰንበት መርዶ ውሎአችንን እንጀምራለን…!! '…በዐማራ መታረጃ ቄራ በሆነው በዚያው በተለመደው | Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

በሰንበት መርዶ ውሎአችንን እንጀምራለን…!!

"…በዐማራ መታረጃ ቄራ በሆነው በዚያው በተለመደው በወለጋ በጄርዴጋ ጃርቴ በኦርሚያ ብልፅግና እና በኦሮሚያ ብልጽግና ፕላን B የዐማራ ማጽጃ ማሽን በሆነው በዳቦ ስሙ ኦነግ ሸኔ፤ በተፈጥሮ ስሙ፣ በመዝገብ ስሙ የኦሮሞ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦነግ) ሠራዊት የተረሸኑ ናቸው። የሚገርመው ደግሞ የኦነግ ፕሬዘዳንት ሁለቱም መቀመጫቸው አዲስ አበባ ነው። ዳውድ ኢብሳ በቁም እስር ሰበብ ይጦራሉ። ቀጀላ መርዳሳ ደግሞ የኢትዮጵያ ባህልና ስፖርት ሚኒስትር ናቸው። አይገርምላችሁም…?

"…የሆነው ሆኖ ከዚህ በታች አስከሬናቸው ተገኝቶ የተቀበሩ ዐማሮችን ስም ዝርዝር እንደሚከተለው አቀርባለሁ። በጎንደር አንድ ሙስሊም ዐማራ እና አንድ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ዕለታዊ ግጭት ሲያደርግ ሃገሪቷን በአፍጢሟ ካልደፋናት የሚሉት እስላማዊ ሚዲያዎች፣ እነ ሙጂብ አሚኖና አህመዲን ጀበል ሁላ በወለጋ ለሚያልቀው የዐማራ እስላም ትንፍሽ አይሉም። አሁን ኦሮሞው ሼክ የሚመሩት የእስልምና መጅሊስም ትንፍሽ አይልም። አብዛኛው በወለጋ የሚያልቁት፣ የሚጸዱትም የወሎ እስላሞች ሲሆኑ በጎንደር በቤተሰብ መካከል ለሚፈጠር ግጭት ትኩረት ሰጥተው እንደሚጮሁት በወለጋ ለሚያልቀው ወሎዬ እስላም ጆሮም አይሰጡት። የዐማራ እስላም ሞት በጎንደርና በወለጋ ይለያያል ወይስ በኦሮሚያ የሚሞት የዐማራ እስላም በቁርዓኑ የተፈቀደ ነው? …ለነገሩ እኔ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ነኝ። በዚያ ላይ ምርጥ ኢትዮጵያዊ። መርጬ አላለቅስም። እንደ ኦሮሞ እስላምና ኡስታዝ ዐማራ ሲሞት እሰይ አልልም። ለማንኛውም የብሩክ አበጋዝ (ዘ ስኳድ) የተስፋዬና የቃልቻው የመንግሥቱ ዘገየ ዘመዶች የሆኑትና ለዘንድሮው ኢሬቻ  ግብር የተሰዉ የታራጆቹን የወሎ ዐማራ እስላሞችንና ጥቂት ኦርቶዶክሶችን ስም ዝርዝር እነሆ። እርማችሁንም አውጦ።

1. ዓለም ይብሬ                 19 ሙሄ ሙሳ
2 ሱፊያን ዩሱፍ                 20 አህሚ ሙሀመድ
3 አሊ አባተ                      21 ያምሬ እሴቱ
4 ሰሚራ ከቤ                    22 መሀመድ ኢብራሂም
5 አህመዲን ወሰን              23 መሀመድ ከዶ
6 አህሜው                        24 ሙሄ ሙሳ
7 በየነ መሀመድ                25 የሱፍ አህመድ
8 ኢብራሂም ሙህዬ            26 ዩሱፍ አመድ
9 ወርቁ ወሰን                    27 ኢብራሂም ሀምዛ
10 ሱፊያን ሽመልስ            28 ኢብራሂም ገደፋው
11 ሀሰን ይመር                 39 ቃሲም ይብሬ
12 ብሬ ምስጋናው              30 ሰዒድ ያህያ
13 ከድጃ ኡመር                31 ኑሬ አህመድ
14 አሊያ ኡመር                 32 ሙህዬ ወርቁ
15 ከስየ ባየ                     33 ወርቁ ሁሴን
16 አህመድ ዑመር            34 ክንዱ ይብሬ
17 ሙሳ ደርሶ                   35 ይብሬ
18 ይማም መንገሻ             36 ሞሚና ስንግል ከአንድ ዓመት ህፃን ልጇ ጋር።

"…በተራ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰው ዓለም ይብሬን እና በተራ ቁጥር 39 ላይ የሚገኘውን ቃሲም ይብሬን ከገደሏቸው በኋላ በእሳት አቃጥለዋቸዋል። በተራ ቁጥር 15 ላይ የተጠቀሰውን ካስየ ባየን ከ5 ቤተሰቦቹ ጋር ነው ያረዱት። "…በተራ ቁጥር 22 ላይ ያለው ይማም መንገሻንም ጭራሽ አንተማ ትግሬ ነህ ተብሎ ነው በአካባቢው የመንግሥት ካድሬዎች እና ሸኔ ተብዬዎቹ በ4 ልጆቹ እና በሚስቱ ፊት የተገደለው።

"…በተራ ቁጥር 32 ሰኢድ ያህ፣ 33 ኑሬ አህመድ እና
ተራ ቁጥር 34 ሙህየ ወርቁ እነዚህ ሦስቱ ደግሞ በጃርቴ የወረዳው የመንግሥት እስረኛ ነበሩ። ከዚያ ከእስር ቤት አስወጥተው ነው የረሸኗቸው። ሲያስሯቸው እናንተ ፋኖ ናችሁ ብለው ነበር። ሰኢድ ያህያ ግን ማንንም የማይፈራ፣ የወረዳ አመራሮች በሚጠሩት ስብሰባ ላይ ሁሉ በግልፅ የሚናገር፣ ለጃርዴጋ ጃርቴ ዐማራዎችም በድምፁ የሚታገል፣ በስብሰባ ላይ በግልፅ ልክልካቸውን የሚነግራቸው፣ እንዲሁም የራሱ የወራዳው ጠንካራ የመንግሥት ሚኒሻ ነበር።

"…ሰኢድ ማለት ከሚኒሻነቱ ባሻገር "እኔ እያለሁ ምንም አትሆኑም በማለት ተስፋ ለቆረጡት ለጃርቴ ዐማራዎች የመኖር ተስፋን ይሰጣቸው የነበረም ጀግና ታጋያቸው ነበር። 4 ግዜ የመግደል ሙከራ የተደረገበት፣ 3 ግዜ በቤቱ እያለ ተከቦ ምንም ሳይነኩት ያመለጣቸውና ሁሉም የሚፈሩት ጀግና ነበር። ነገር ግን በመጨረሻ በሸኔ ስም መግደል ሲያቅታቸው ሕግ በማስከበር ሰበብ ራሱ መንግሥት ትፈለጋለህ ብሎ ጠርቶት፣ መሳሪያህን አውርድ ብለው አስወርደውት፣ እስርቤት ካስገቡት በኋላ ከእስር ቤት አውጥተው ከሁለት የዐማራ እስረኞች ጋር ረሽነዋቸዋል።

"…ጃርቲ ወረዳው ወስጥ ሦስቱንም ከገደሉ በኋላ    የሰይድ ያህያን አስከሬን ግን ለይተው በማውሰድ በሰንደቅ ዓላማ መስቀያው ብረት ላይ ሰቅለው ክቡር በሆነው አስከሬኑ ስር እንደ ጉድ ሲዘፍኑ፣ ሲሳለቁ ውለዋል።

"…ቆይቼ እመለሳለሁ…!! እስከዚያው እንደተለመደው ነፍስ ይማር እንበል።