Get Mystery Box with random crypto!

እግዚአብሔር ሲገድሉትም የዋህ ነው፣ ሳይገለጥ ይታወቃል፡፡ ሳይታወቅም ግልጥ ነው፡፡ ሲርቁት | ✿✟ የ҈ ዳ҈ ዊ҈ ት҈ ዜ҈ ማ҈ ✟✿

እግዚአብሔር

ሲገድሉትም የዋህ ነው፣
ሳይገለጥ ይታወቃል፡፡
ሳይታወቅም ግልጥ ነው፡፡
ሲርቁት ይቀርባል፣
ሲጠሉት ይወድዳል፡፡
አጥሩ ነበልባል ነው ቤቱ ውኃ ነው


በነፋስ ክንፍ ይሄዳል፡፡

መላእክቱንም ሥጋ የሌላቸው ረቂቃን አደረጋቸው፤

የሚያገልግሉትንም የእሳት ነበልባል አደረጋቸው፡፡
መሬትን የሚመለከታት፣ እንድትንቀጠቀጥ የሚያደርጋትም እርሱ ነው፡፡

ሲነካቸውም ተራሮች ይጤሳሉ።

ዓለም ሁሉ በፊቱ የተመዘነ ነው፡፡

ስለዚህም እርሱ ራሱን ሲገልጥ የእስራኤልን ቅዱስ እኔን በማን ትመስሉኛላችሁ?

ሰማይም እንደ ብረት ትጸናለች፤
መሬትም እንደ ልብስ ታረጃለች።

በውስጧ የሚኖሩትም ሁሉ እንደ አንበጣ ናቸው እንደ ዝናም ነጠብጣብም ናቸው። እንደምትሰበስብ የዓይን ሚዛንም ናቸው፡፡ የአንዱን ሚዛን ጉድለቱን የሚጨምር ትንሽ ሚዛንም ይህ ነው፡፡ በእርሱ ዘንድ የዚህ ዓለም ምሳሌ ሆነው ከተባለው ጋር እኩል ይሆን ዘንድ፡፡ ነቢዩም ይህን ተገንዝቦ «ሰውነቴ በአንተ ዘንድ እንደ ኢምንት ነው አለ፡፡

ስለገናናነቱ መልካምን ያደረገ የእርሱን ነገር ጠንቅቆ መናገር ፈጽሞ አይቻለንምና ዝም እንበል፣ ክብር፣ ቡራኬ፣ ምስጋና በፍጥረታቱ፣ በዓለማቱ ሁሉ ለአብ ለወልድ፣ ለመንፈስ ቅዱስ ይሁን፡፡ አሜን፡፡