Get Mystery Box with random crypto!

መግቦተ እግዚአብሔር

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemariyannen — መግቦተ እግዚአብሔር
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemariyannen — መግቦተ እግዚአብሔር
የሰርጥ አድራሻ: @zemariyannen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.62K
የሰርጥ መግለጫ

"ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እሱን ያፈርሰዋል ፤የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ"
1ኛ ቆሮ 3፥17
#የማህበሩ_አላማ
የኦርቶዶክስን ቀኖና፣ዶግማ እንዲሁም ትውፊት በጠበቀ መንገድ አስተማሪ የሆኑ መዝሙሮች፣አስተምሮቶች እንዲሁም ስብከቶች እናቀርባለን።
@zemariyannengp
@Zegebreal7
ሼር በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ!!

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-02-28 12:44:05
535 views.........., 09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-28 12:11:04
568 views.........., 09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-26 10:23:01
ገብርኤል ሆይ ምስጋናን በዝማሬ ድምፅ ለሚያሰማ (ለሚያመሰግን) ኅሊናህ ሰላም እላለሁ። የሥጋዊ ባሕርይ ክፍለ አካል ግን በባሕርይ የሌለ ነው። ገብርኤል ሆይ የደኅንነት መልአክ ነህና እኔን አገልጋይህን ከችግር አውጣኝ። ይልቁንም ጠላቴ ሰይጣን የመቅሠፍት እሳት ወላፈኑን በኔ ላይ በነዛ ጊዜ ፈጥነህ በክንፎችህ ጋርደኝ።
579 viewsĎĔĔPËŔ, 07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-25 21:23:38 መስቀል እና ማማተብ

ዛሬ ደሞ ከአቡነ ሽኖዳ" አንፃራዊ ትምህርተ መለኮት "መፅሀፉቸው ላይ ተነስተን እንማማራለን ።ጌታችን በአገልግሎቱ ወቅት /ከመሰቀሉ በፊት / ለመስቀል ታላቅ ትኩረት ሰጥቷል ። ይህንንም ሲገልፅ "መስቀሉንም የማይዝ በኀላዬም የማይከተለኝ የእኔ ሊሆን አይገባውም ።/ማቴ10:38/ እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ ። (ማር 834)

መስቀል የመላዕክት እና የሀዋሪያት የአገልግሎታቸው መሰረት ነው ። የጌታችንን መነሳት ለሴቶቹ ያበሰረው መልአክ " እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለውና " / ማቴ 28:5/ጌታ የተነሳ ቢሆንም መልአኩ "የተሰቀለው" ብሎ ጠራው ።ቅዱስ ጵጥሮስም አይሁድን ሲሰብክ "እንግዲህ እናንተ የሰቀላችሁትን ኢየሱስን.. /ሀዋ ስራ 2:36/ ። መስቀል የሀዋሪያት ክብራቸው ነው ። ለዚ ነው ጳውሎስ "ከጌታችን ከኢየሱስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከኔ ይራቅ "(ገላ6:14)ያለው

በመስቀል አምሳያ ስናማትብ የተሰቀለው ገንዘቦች መሆናችንን እንገልፃለን ። በማማተብ ፣ መስቀልን በአንገታችን በማሰር ፣ በጌጣጌጦቻችን በመቅረፅ ፣ በእምነት ቦታዎቻችን ላይ ከፍ አድርገን በመስቀል ለእኛ ሲል የተሰቀለው መሆናችንን እንገልፃለን ።እኛ በቃላችን ሳንናገር ሰዎች እኛን በማየታቸው ብቻ ስለ እኛ እምነት የተሰበኩ ይሆናሉ ።ስናማትብ "በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሃዱ አምላክ " እንላለን እንጂ ዝም ብለን አናማትብም

ስለዚህ ባማተብን ቁጥር እስከ ዘለዓለም አንድ አምላክ በሆነ በቅድስት ስላሴ ማመናችንን እንገልፃለን ። ስናማትብ በስጋዌና በተደረገልን ካሳ ማመናችንን እንመሰክራለን ። ስናማትብ እጃችንን ከላይ ወደ ታች ከግራ ወደ ቀኝ በመውሰድ እናማትባለን ። በዚህም እግዚአብሔር ከሰማያት መውረዱንና ሰዎችን ከግራ ወደቀኝ ፡ ከጨለማ ወደ ብርሃን ማሻገሩን እናስታውሳለን ።ሰይጣን ስለሚፈራው እናማትባለን ። ከአዳም ጀምሮ የተደረገው የሰይጣን ትግል በመስቀሉ ከንቱ ሆነ እግዚአብሔር ወልድ በደሙ ዋጋውን ከፍሎ የሰዎችን ኃጢያት አስተሰረየ

ለሚያምኑትና ለሚታዘዙት ሁሉ ህይወትን ሰጠ ። ስለዚህም ሰይጣን መስቀል ባየ ቁጥር በመስቀል የተደረገውን ታላቁን መዋረዱን ፣ መሸነፉንና ያጣውን ምርኮ በማስታወስ ይሸሻል ።በማማተብ ቡራኬ እንቀበላለን ። በመስቀሉ የአዲስ ህይወት በረከትና የአካሉ ክፍሎች የመሆን በረከትን ሰጠን ። ከዚህም በተጨማሪ የአዲስ ኪዳን ፀጋዎች የተገኙት ከመስቀል ነው

ካህናትም ለመባረክ መስቀልን የሚጠቀሙት ቡራኬው ከእኛ ሳይሆን ከጌታ መስቀል ነው ለማለት ነው ። ወስብሀት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ወትረ ጊዜ ወበኩሉ ሰዓት አሜን
592 views.........., 18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-22 14:13:44
የካቲት ፲፮ (16)
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ዓመታዊ ክብረ በዓል (#ቃል_ኪዳን_ለተቀበለችበት) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡

፠ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ፤ ፈለገ እሳት ወደይን እምአስጠመ ኵሎ፡፡ (ድንግል ሆይ ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የሲኦል እሳት ባሰጠመን ነበር፡፡) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሲዖልን ካየች በኋላ ስለኃጥአን እጅግ እያዘነች ኖረች ፠ የካቲት ፲፮ ቀንም በጎልጎታ ቦታ ቆማ ወደ ልጇ እንዲህ ብላ ለመነች፡፡
፠ጸሎትና ልመናዬን ስማኝ ቃሌንም አድምጥ እኔ እናትህ አገልጋይህ የምለምንህን ይህ ነው፡፡ ፨ መታሰቢያዬን ለሚያደርጉ፣ ፨ አብያተ ክርስቲያኔን ለሚሠሩ፣ ወይም ፨ ለታረዙ ለሚያለብሱ፣ ለተራቡ ለሚያጠግቡ፣ የተጠማውንም ለሚያጠጡ (በስሜ ለድሆችና ለችግረኞች ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጡ)፣ ፨ የታመመውንም የሚጎበኝ፣ ያዘነውንም የሚያረጋጉ፣ የተከዘውንም ደስ የሚያሰኙ ወይም ፨ ምስጋናዬን ለሚጽፉ፣ ልጆቹንም በስሜ ለሚሰይም፣ ፨ በበዓሌም ቀን በማኅሌት ለሚያመሰግን አቤቱ በዓይን ያልታየውን በጆሮ ያልተሰማውን በጎ ዋጋ ስጣቸው፡፡ ፨ በአማላጅነቴም የሚተማመኑትን ሁሉ ከሲዖል ነፃ አድርጋቸው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን ረሃብና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ የሰጠሁሽን ቃልኪዳን እንዳይታበይ በራሴ በባሕርይ አባቴ በአብ በባሕርይ ሕይወቴ በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣት፡፡

መልካም በዓል
846 views.........., 11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-17 20:27:26
686 viewsĎĔĔPËŔ, 17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-13 21:42:31
እንኳን አደረሳችሁ ፆሙን የሀጢያት መደምሰሻ የሰይጣን ድል መንሻ የመንግስተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን አሜን!!!
844 views.........., 18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-13 07:00:02 የነነዌ ሰዎችና እኛ

ከነነዌ ሰዎች በላይ ማን ክፉ ነበር? ከእነርሱ በላይ አላዋቂስ ማን ነበር? ("ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ" ተብለው ተጠርተዋልና፡፡) ነገር ግን እነዚህ አሕዛብ፣ እነዚህ አላዋቂ፣ እነዚህ አንድ ሰውስ እንኳን የጥበብን ነገር አስተምሮአቸው የማያውቁ፣ እነዚህ ከማንም ይኹን ከማን እንደዚህ ዓይነት ትእዛዝን ያልተቀበሉ ሰዎች ነቢዩ፡- “በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች” ሲል በሰሙት ጊዜ ክፉ ልማዳቸውን ኹሉ በሦስት ቀናት ውስጥ አስወግደዋል (ዮና.3፥4)፡፡

ዘማዊው ንጹህ፣ ደፋሩ ትሑት፣ ስስታሙና ጨቋኙ ራሱን የሚገዛና ደገኛ፣ ሐኬተኛውም ትጉህ ኾነ፡፡ እነዚህ ሰዎች በርግጥ ያሻሻሉት ክፋታቸውን ኹሉ እንጂ አንዱን ወይም ኹለቱን ወይም ሦስቱን ወይም አራቱን አይደለም፡፡ “እንዲህ የሚልስ የት አለ?” ብሎ የሚጠይቅ ሰው ሊኖር ይችላል፡፡ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስለታለሁ፡- እነርሱን ሲወቅሳቸው የነበረውና፣ “የክፋታቸውም ጩኸት እስከ አርያም ድረስ ወጥቷል” ብሎ የተናገረው ነቢይ መልሶ ደግሞ የዚሁ ፍጹም ተቃራኒ የኾነን ምስክርነት አስቀምጧልና፤ እንዲህ ሲል፡- “እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደ ተመለሱ ሥራቸውን አየ” (ዮና.1፡5፣ 3፡10)፡፡ ተመልከት! ከዝሙት ወይም ከአመንዝራነት ወይም ከሌብነት ራቁ አላለም፤ “ከክፉ መንገዳቸው” እንጂ፡፡ እንዴትስ ከዚያ ሊርቁ ቻሉ? ይህን እግዚአብሔር ያውቋል እንጂ ሰው ሊመረምረው አይችልም፡፡

እንግዲህ አሕዛብ በሦስት ቀናት ውስጥ ብቻ ክፋታቸውን ኹሉ ማስወገድ ከቻሉ፥ ለአያሌ ቀናት የተመከርንና የተዘከርን እኛ ግን አንዲት ክፉ ልማድን ለምሳሌ መሐላን ሳናስወግድ ስንቀር ልናፍር አይገባንምን? ከዚህም በላይ እነዚህ ሰዎች ቀድሞ ክፋታቸው ጣሪያ ደርሶ ነበር፤ “የክፋታቸውም ጩኸት እስከ አርያም ድረስ ወጥቷል” የሚለውን ስትሰማ ከክፋታቸው ብዛት በቀር ሌላ ምንም ልትገነዘብ አትችልምና፡፡ ነገር ግን በሦስት ቀናት ውስጥ ወደ መልካም ምግባር ፍጽምና መድረስ ተችሏቸዋል፡፡ ፈሪሐ እግዚአብሔር ባለበት ቀናት ወይም የጊዜ ብዛት አያስፈልግምና፡፡ በተቃራኒው ይህ ፍርሐት በሌለበት ደግሞ የጊዜ ብዛት ምንም ጥቅም የለውም፡፡

የዛጉ ብረቶችን በውኃ ብቻ የሚያጥባቸው ሰው ምንም ያህል ጊዜ እነርሱን በማጠብ ቢያሳልፍም እነዚያን ዝገቶች ኹሉ ማስለቀቅ አይቻለውም፡፡ ወደ እሳት ጨምሮ የሚያወጣቸው ሰው ግን አዲስ ከተሠሩ ብረቶችም ጭምር ሳይቀር እጅግ ጽሩያን ያደርጋቸዋል፡፡ በኃጢአት የዛገ ልብም እንዲሁ በትንሽ በትንሹና በግድየለሽነት ኾኖ ዕለት ዕለት ንስሐ ቢገባም ምንም ጥቅም አያገኝም፡፡ ራሱን ወደ እቶን - ይኸውም ወደ ፈሪሐ እግዚአብሔር የሚጥል ከኾነ ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ኹሉንም ማስወገድ ይቻለዋል፡፡

(በእንተ ምክንያተ ሐውልታት፥ ፳:፳፩ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው)
1.3K views.........., 04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-12 10:31:09 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ጸጋና ሰላም

“ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን ።” ኤፌ. 1፡2

ጸጋና ሰላም ከእግዚአብሔር አባትነት ከክርስቶስ ጌትነት ካልሆነ ከማንም አይገኙም ። ጸጋው የእምነታችን መሠረት ፣ ሰላሙ የእምነታችን ፍሬ ነው ። ጸጋውን ለማግኘት ማመን ፣ ሰላምን ለማግኘት ማፍራት ግድ ይላል ። ቃሉ፡- “ለክፉዎች ሰላም የላቸውም” ይላል ። ኢሳ. 48 ፡ 22 ። ጸጋው ልብስ ነውና ለተራቆተው ፣ ሰላም ጽናት ነውና በገነት ጫካ ለተደበቀው ለአዳም ያስፈልጋል ። ዛሬም ብዙዎች ዕራቁታቸውን አሉ ። በማይሸፍናቸው ወዳጅ ፣ ትዳር ፣ አገርና ወገን ውስጥ አሉ ። ሰላምን ለማግኘትም በሱስ ውስጥ ፣ ተአምር አድራጊ ነን በሚሉ ቀሚስ ውስጥ የተደበቁ ብዙዎች ናቸው ። ጭንቀታቸው ስለበዛ መጮህና መውደቅ ፈልገው በየመድረኩ ዋይ የሚሉ ሰላም አጥተው ነው ። “ለራስ ምታት ጩህበት ፣ ለሆድ ቁርጠት ብላበት” እንዲሉ ። ራስ ምታት የውስጥ ጩኸት ነውና ሲጮሁበት ፣ ቁርጠትም ባለቤቱን ከሚቆርጥ ከሚቆርጠው ምግብ ሲላክለት ጥሩ ነው ብለው ይመስላል ። በርግጥም ጭንቀት በመጮህ ይታገሣል ። በየሚዲያው ሲጮሁና ሲሳደቡ የሚውሉ ጭንቀት ያለባቸው ሰዎች ናቸው ። የውስጡን ጩኸት በውጭ ጩኸት ሊያዳፍኑት ሙከራ ያደርጋሉ ። ሰላምን ለማግኘት የሰው ልጅ ብዙ እየጣረ ነው ። ጸጋ ሁኖ የሚሸፍን ፣ ሰላም ሁኖ የሚያሳርፍ ግን እግዚአብሔር ብቻ ነው ።

ጸጋና ሰላም የብዙዎች ጥያቄና ፍለጋ ነው ። ብዙ ሰው በነጻ መወደድን ይፈልጋል ። ልጆቹን እንኳ በሚሰጣቸው ገንዘብና ሀብት ፍቅራቸውን ለመግዛት የሚሞክር አያሌ ወላጅ አለ ። ልጆቹ ግን የበለጠ እየጠሉት ይመጣሉ ። ፍቅር በፍቅር ብቻ እንጂ በገበያ አይገኝም ። ሚስቱንም በስጦታ ብዛት እንድትወደው የሚፈልግ ካለ እርስዋም ይህን ካሰበች ከአንድ የዝሙት አዳሪ አትለይም ። የጋራ ፍቅር ፣ ፍቅርን ያጸናል ። መልሰን ካልወደድነው እግዚአብሔር እንኳ እኛን መውደዱ ብቻውን ከገሀነም አያድነንም ። ፍቅር የጋራ ነው ። ፍቅር በፍቅር ብቻ ይገኛል ። ፍቅር ራሱን ይሰጣል ። አፍቃሪ መፈቀር ይሻል ።
575 views.........., 07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-06 10:59:29 #በደልን_እርሱ

በቋንቋ የማይግባቡት እንስሳት አብረው ይኖራሉ ። በቋንቋ የሚግባባው የሰው ልጅ ፍጥረት ግን ቋንቋውን ለመንቋቆር እየተጠቀመበት አብሮ መኖር ተስኖታል ። እንስሳት እንደ ሰው ቢያስተውሉ እና ቢናገሩ "የመኖሪያ ቦታ እንቀያየር" የሚሉን አይመስላችሁም ? ።

ወንድም ወንድሙን ስለመጥላቱ በእግዚአብሔር ፊት የትኛውም ምክንያት ተቀባይነት እንደሌለው ስንቶቻችን እናውቃለን ግን ? ። እግዚአብሔር ለጥላቻ ምክንያት ቀርቦለት ተቀብሎ አያውቅም አይቀበልምም ።

እና ምንድነው መፍትሄው ?

የሰውን በደል መርሳት ! ። የሰውን በደል ለመርሳት ፍቃደኛ ያልሆነ ሰው መቼም አይረሳውም ። ፍቃደኛ የሆነ ሰው ግን ግዜው ቢረዝምም እንኳን ትክክለኛ ጤንነቱን እያገኘ ይመጣል ። ጸሎት ለሁሉም ነገር መፍትሄ ነውና ለመርሳት ጸልዩ
651 viewsĎĔĔPËŔ, 07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ