Get Mystery Box with random crypto!

ሐምሌ 19 እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል አደረሳችሁ:: ☞ በዚህ ዕለት ቅዱስ ገ | መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

ሐምሌ 19
እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል አደረሳችሁ::
☞ በዚህ ዕለት ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት እየሉጣን
ከእሳት አድኗቸዋል::
✞ ቅዱስ ቂርቆስ ሀገሩ ሮም/ጣሊያን/ አንጌቤን ሲሆን አባቱ ቆዝሞስ እናቱ ደግሞ ኢየሉጣ ትባላለች፡፡
በዘመነ ሰማዕታት በጨካኙና በአረመኔው በዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ
መንግሰት በ ፫፻፫ /303/ ዓ.ም አብያተክርስቲያናት ይውደሙ አብያተ ጣዖታት ይስፋፉ የሚል አዋጅ ታወጀ፡፡ በዚህ ምክንያት ብዙ ክርስቲያኖች ተሰደዱ ቅድስት ኢየሉጣም የ ፫ /3/ ዓመት ሕጻን ልጇን ቂርቆስን ይዛ ወደ ኢቆንዩን የምትባል ከተማ ሸሸች፡፡
☞ መስፍነ ብሔሩ እለእስክንድሮስ ክርሰቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ ቢላት
"ዓይን እያለው ለማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሰርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም" አለች::
አይሆንም ካልሽማ በሰይፍ ትቀጫለሽ ብሎ አስፈራራት እስኪ ይህን ሕፃን ጠይቀው አለችው አንተ ሕፃን ወርቅ እሰጥሀለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ አለው::
መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና "ራሳቸውን ማዳን ለማይችሉ ርኩሳን ጣዖታትህ አልሰግድም" አለው::
ተበሳጭቶም የብረት ጋን ውስጥ ውኃ አስፈላ የፍላቱም ድምፅ እንደ ክረምት ነጎድጓድ 24ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር::
ሊከቷቸው ሲወስዷቸው እየሉጣ ልቧ በፍርሀት ታወከ ሕፃኑ ቂርቆስም እናቴ ሆይ አትፍሪ አናንያን አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ እኛንስ ያድነን የለምን ? እያለ ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ ወደ ጋን ውስጥም ከተቷቸው::
✞ ያን ጊዜ ጌታ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ በበትረ መስቀሉ ውኃውን አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል::በወጡም ጊዜ ልብሳቸው ሳይበሰብስ ሰውነታቸው ሳይሸበሸብ ቢያዩ ከአሕዛብ ብዙዋቹ አምነው ሰማዕትነት ተቀብለዋል::
✞የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ፈጥኖ ተራዳኢነት የቅዱስ ቂርቆስና የቅድስት እየሉጣ ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን::
<<ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>
<<ወለ ወላዲቱ ድንግል>>
<<ወለ መስቀሉ ክቡር>>