#ታኅሣሥ_6
ዛሬ በደጇ ወድቀን የምንለምናት ሁሉ በህይወት ስጋ በመከራ ሆና አምላክነቱን የመሰከረችለት አምላክ ዛሬ በትውልዱ ሁሉ እምነቷን በእርሷ ስም ለተማፀኑ ላጣ በመስጠት ሲመሰክርላት ይኖራል ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ። ዛሬ የብዙዎቻችን ችግር በእምነት መኖርን አለማወቅ ነው አንዳዶቻችን ያመነው እምነት ምድራዊ ፍላጎታችንን እስካላሟላ ድረስ ሊያሟላልን የሚችል እምነት ስንቀያይር እንኖራለን ቁስ እስካልያዝን እስካልሰበሰብን ድረስ ምኑን አምንኩ እያልን ስናማርር እንኖራለን ። ትንሽ ሰርተን ብዙ እንፈልጋለን ። ክርስቲያን የዚህን ምድር ፍላጎት ከውስጡ ሲያወጣ ብቻ ነው የሰማይ ቤቱ ሙሉ ሚሆንለት ። ሰማእታት በእውነት የዚህን ምድር ሁሉን ነገር እንደናቁ እናስተውል ።
የሰማዕቷ የቅድስት አርሴማ አማላጅነቷ አይለየን !!
~ዲያቆን ፍፁም ከበደ~