Get Mystery Box with random crypto!

~ኅዳር 21~ እንኳን ለታቦተ ጽዮን አመታዊ በአል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ **በዚች በኅዳር 21 | ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

~ኅዳር 21~

እንኳን ለታቦተ ጽዮን አመታዊ በአል በሰላም አደረሳችሁ፡፡

**በዚች በኅዳር 21ቀን ነቢዮ ዘካርያስ በተቅዋመ ማኅቶት አምሳል ያየበት ፡፡

**እንዲሁም ቀዳሚ ምኒልክ ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የገባበት ፡፡

**እንዲሁም ታቦተ ጽዮን በዮዲት ጉዲት ገዜ በዝዋይ ደሴት ቆይታ ሰላም ሲኾን ተመልሳ
አክሱም የገባችበት ዕለት ነው ፡፡

**በተጨማሪም አብርሀና ወ አጽበሐ(ንጉስ ኢዛና እና ሳይዛነ) በአክሱም ከተማ የታቦተ ጽዮን
ቤተ መቅደሱን ሠርተው ቅዳሴ ቤቱን ያከበሩበት የበአሉ መታሰቢያ ኅዳር 21ቀን
ነው፡፡

በዚች በኅዳር 21 ያረገችው ታአምር ይህ ነው ፍልሰጥኤማውያን ጽዮንን
ማርከው ወደ አዛጦን ወስደው በደጎን ሥር አድርገው ኼዱ፡፡ በነጋው ቢገብ
በግንባሩ ተደፍተው፡፡ አገኙት፡፡ እንደ ነበረው አድርገው ኼዱ፡፡ በነጋው ቢመጡ
እጅ እግሩ ተቁራርጦ ደረቱ ቀርቶ አገኙት፡፡ ከዚያ ወደ ጌት ወደ ምትባል ቦታ
ሰደዷት፡፡ ከዚያም ወደ አስቀሎና ኢሎፋሊ እየተዘዋወረች ለ7ወር ተቀመጠች፡፡


በኃላ ባደረገችው የኀይልና የመቅሰፍት ተአምር ቀንበር ያልተጫነባቸው
ጊደሮች ጠምደው በዐዲስ ሠረገላ ጭነው ካሳ በአይጥ ምስል ወርቅ ሠረተው
ላኳት፡፡
ጊደሮችም ያለ ነጅ ወደ አስራአል ሀገር አምጥተው በቤትሳሚስ ከኢያሱ ዕርሻ
አጠገብ ደርሰው ቆሙ፡፡ የቤተሳሚስም ሰዎች ሠረገላውን ፈልጠው ላሞቹን
ዐርደው መሥዋዕት አቅርበዋል፡፡ ከዚያ ወደ አሚናዳ ቤት መጥታ አልዓዛር
እያገለገት ዳዊት አስኪያመጣት ድረስ 7አመት ድረስ ተቀምጣለች፡፡

(~መድበለ ታሪክ~)


እንኳን አደረሳቹሁ የቻናሌ ቤተሰቦች

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ኅዳር 20 2015 ዓ.ም