Get Mystery Box with random crypto!

የዚልሂጃ ወር የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት ታላቅነት  አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ የማለባቸው ቀናት መ | ሂዳያ - هداية - Islamic Guidance

የዚልሂጃ ወር የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት ታላቅነት

 አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ የማለባቸው ቀናት መሆናቸው

አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ

وَالْفَجْرِ ﴿١﴾ وَلَيَالٍ عَشْرٍ ﴿٢ وَالشَّفْعِ وَالْوَتْرِ

 
“በጎህ እምላለሁ። በዐሥር ሌሊቶችም። በጥንዱም በነጠላውም።”
 (አል-ፈጅር 89፤ 1-3)

ከጃቢር ኢብኑ ዐብዱላህ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ
(صلى الله عليه وسلم)
እነኚህ አሥር ቀናቶች የትኞቹ እንደሆኑ በሚያመላክተው ሀዲሣቸው ውስጥ እንዲህ ብለዋል፡-

《العشر عشر الأضحى، والوتر يوم عرفة، والشفع يوم النحر》

“አሥሩ ማለት አሥሩ የአድሃ ቀናት ናቸው። ‘ወትር’ /ጥንዱ/ የተባለው የዐረፋ ቀን ሲሆን ‘ሸፍዕ’ /ነጠላው/ ማለት ደግሞ የነህር /የእርዱ/ ቀናት ናቸው።” ብለዋል። ኢማም ነሣኢ እና ሃኪም በሙስሊም ሰሂህ ሀዲስ ነው ብለውታል።

ኢማም በይሀቂ ከዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይር እንደዘገቡት ደግሞ:-

《ليالٍ عشر، العشر الثماني، وعرفة، والنحر》
“አሥርቱ ሌሊቶች የመጀመሪያዎቹ ስምንቶቹ፣ የዐረፋ ቀን እና የእርድ ቀን ናቸው።” ብለዋል።

https://t.me/abu_abdurahman5