Get Mystery Box with random crypto!

HOME || ቤት 🏚

የቴሌግራም ቻናል አርማ yonis_home — HOME || ቤት 🏚 H
የቴሌግራም ቻናል አርማ yonis_home — HOME || ቤት 🏚
የሰርጥ አድራሻ: @yonis_home
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 721
የሰርጥ መግለጫ

Feel at Home!
@yonis_home_bot

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-16 09:22:39 Congratulations Yonathan!

You're there! You have battled, hassled, fought and strived to be here. You're one hell of a person መድኀኒዓለምን! I'm lucky to be you! You deserve every piece of success. አንዳንዴ ታናደኛለህ እንጂ እኮ I can't hate you

Keep your head up sir!
217 views06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 22:08:57
Let's shout out to our new members
283 views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 00:39:45 What's the only good thing about living in Kality?

ሰዎች ድግስ ባትጠራቸው አይቀየሙህም። እንደውም ብትጠራቸው ነው የሚቀየሙህ!
405 views21:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 16:05:41 በእውነት I'm so tired of being an Ethiopian! ይቺ ሀገር ደክማኛለች!
ሶስት ||| ምሳሌዎችን ላንሳ...


ፖለቲከኞች የቀዳደዷትን ሀገር "አዝማሪዎች" ሊሰፏትና ሊያበጇት ይባትላሉ። በዚህ በቀውጢ ጊዜ ብዙ የሐይማኖት አባቶች ግድ ሰጥቷቸው ሲሰብኳቸው የማይደመጡት እምነት፣ ተስፋ እና ፍቅር ከሞዛቂዎቹ አንደበት ላይ ተሰይመዋል። "ዘማሪዎች" በመዝሙራቸው ያልሰበኩን ሕብረት በ"ዘፋኞች" እየተቀነቀነ ነው። ግን የኛ ነገር "የአህያ ስጋ አልጋ ሲሉት አመድ" አይነት ነገር ሆኖ ማር አልጥማችሁ ካለን ከራረመ መሰል። ትልልቅ ሚድያዎች ሳይቀር እጅ እጅ የሚሉ ጥራዝ-ነጠቅ conspiracy theories በመንደር ባልቴት ወግ ይጠረቅባቸዋል። ስም አልጠራም ግን እንደ አብይ ይልማ ያሉ (ማነው ግን ይቺን ሀገር ደህና አብይ አይውጣብሽ ብሎ የረገማት?) ያልነቁ "አንቂዎች" የዚህን ህዝብ ደካማ ጎን ተጠቅመው የሌለ እየነገዱበ ነው። ይሄ አይነፋም! ሰዉም ቆም ብሎ ማሰብ አለበት። ከዚህ በኋላ ያለውን ትውልድ እሳቤዎች የምትሞግተው ሎጂካል በሆኑ ሙግቶች እንጂ casual የሆኑ gesture'ሮችን ከሆነ ideal ከሆነ እና real ይሁን፣ አይሁን ከማይታወቅ secret Society ጋር በማቆራኘት ያንን ምልክት ያሳዩትን ሰዎች ስም በማጠልሸት አይደለም። ደግሞ በምን ሂሳብና ስሌት ነው በሙዚቃዎቻቸው ፍቅርና አንድነትን የሚሰብኩ ሰዎች ከጀርባው ሰይጣን ይዘውረዋል ብለው ከሚያሙት ኅቡዕ ማህበር ጋር አብረው የሚሰሩት? ነው ወይስ ሰይጣን ይሄን ሁሉ ዘመን ጥላቻ ሲሰብክ ኖሮ ስላልተሳካለት አሁን ፍቅርን መስበክ ጀመረ? እና ባሻ conspirator... አንተ መብትህ ነው ባሻህ ነገር የማመን! ግን የሰውን ስም ያለበቂ ማስረጃ በአደባባይ ማጥፋት ነውር ብቻ ሳይሆን ወንጀልም ነው! አጉል የባልቴት ተረትህን ትተህ ትውልዱን የሚጠቅም ነገር መስራት ይበጅሀል። አስሬ "ኢሉ||ሚናቲ፣ የሳጥናኤል ጎል" እያልክ አታዝገን።
And about the album? አላውቅም! አልሰማሁትም! ዘፈን ኃጢአት ነው


ቢንያም ኢሳያስ ይባላል። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጥቁር አንበሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ትምህርቱን እየተከታተለ 5ኛ ዓመት ደርሷል። በዛ ላይ በውጤት ምዘናም 3.8 GPA ነው ያስመዘገበው። ግን ከዚህ በኋላ ትምህርትህን መከታተል አትችልም ብሎታል። ለምን? ምክንያቱም ቢንያም ከልጅነቱ ጀምሮ አብሮት የኖረ የአካል ጉዳት ስላለበት።

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ብዙ የተማሩ መሀይማን እንዳሉ ሰምቼ ሳይሆን አልፌበት አይቻለሁ። መቼም ከዚህ ልጅ ኬዝ በላይ ይሄን የሚያስረግጥ ሌላ አስረጂ አያሻም። 5 ዓመት ሙሉ ዝም ብሎ አሁን ጥቂት ጊዜ ሲቀረው "ከዚህ በኋላ መማር አትችልም! ከፈለክ ሌላ ትምህርት ከ0 ጀምር" ማለት ምን ማለት ነው? የሰው እድሜ ቀልድ ነው? በዛ ላይ ጉዳቱ ከመስራት እንደማያግደው እየተናገረ ነው... አይሆንም ከተባለም ሁለት እጅ የማይጠይቁ እንደ ሳይካትሪ ወይም ፐብሊክ ኸልዝ ያሉ ፊልዶች ላይ መድቡኝ ቢልም አይሆንም ብለውታል። ለምን? በየቢሮው የተሰገሰጉ ድልብ ደናቁርት ናቸውና።


ትላንትና የቴዲ አፍሮ አድናቂዎች ልደቱን አስታከው ደም ሊለግሱ ደም ባንክ ሄዱ አሉ (btw we all can agree that he got the most annoying fan base, right? ) ከዚያ ልክ እዛ ሲደርሱ "ከበላይ አካል የመጣ ትዕዛዝ ነው" ብለው ከለከሏቸው አሉ። Yeah, ደም እንዳይለግሱ ከለከሏቸው (ተሰማኝ በዉነት ተጠጥቻለሁ አለ ሸዋፈራሁ ) C'mon ብልፅግና... you're more than this! I mean I always think you as dűmb but not this much. You always surprise us becoming ďumber and đumber. ደም አትለግሱ በማለት ማንን ነው የጎዳው? ቴዲን? አድናቂዎቹን? ወይስ በየሆስፒታሉ ያሉትን ታማሚዎችና በየጦርነቱ የቆሰሉትን ወታደሮች? እንደውም ብልጥ ቢሆኑ ከሁለቱም እጆቻቸው ነበር ማስለገስ የነበረባቸው


እንዲህ በሆነው ባልሆነው ካልተቃጠልን ብርዱ እንደው አይገፋም!
401 views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 12:57:58

ስናስብ *አለ አይደል....*

ፀዴ ፀዴ ሀሳቦች ያሉበት ቻናል ነው እና ብትቀላቀሉ ታተርፋላችሁ
407 viewsedited  09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 12:53:09 ዞርን
አሰስን
ዳሰስን

በመጨረሻም አጥፊውን ከፊታችን አገኘነው።

አንተ ነህ አልነው።

ጣታችንን ጠቆምንበት።

መስታወት ፊት ቆመን.....

@snasb_hasab
388 views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 19:17:05 Graduation is in a week and here I'm lying on my bed 24/7 አንድ ደህና ፎቶ እንኳን ሳልነሳ

#ድንዛዜ_አልበዛም_ወይ_መፋዘዙ
#እዋዋን_ማንንም_አልሰማም_Cause_Im_deaf
#አይ_አም_ሶ_ግላዲ
#ግሎሪ_ቱ_ጋዲ(ሳ)
#ወጡ_ሳይወጠወጥ_ወስከምባው_ቂጥጥ
#ከላይ_ያሉት_ናቸው_አላሰራም_ያሉኝ
#አይደገስም!
#እርጉማኑ_ሊመርቁኝ_ነው
#አንተ_እዚህ_Add_አስብሉኝ_ትላለህ_እኔ_ኮርስ_Add_አደርጋለሁ
#We_aint_the_same_bro
371 views16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 03:48:41
475 views00:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 03:48:14 የድኩማኑ መልዕክት
- ምዕራፍ 0 -

እንግዲህ ምን እንላለን? ማንነታችን የተገለጠ አይደለምን?

ዛፍ ላይ እንደበቀለ ዱባ፣ እንደ ጣፋጭ ቅል፣ ወደተራራ አናት እንደሚፈስ ወንዝ፣ እንደበራሪ እባብ፣ አይነት ትርጉም-አይሰጤነት ሰፍሮብናል!

ነፍሳችንና ስጋችን ምን እና ምን ናቸው? ከስሱ ልብ እና ከደንዳና ቆዳ ለምን አዛንቆ ፈጠረን? ውስጣችን በእምባ ማዕበል ሲናጥ ለምን ዐይናችን ዘለላ እምባ ማዠት ያቅተዋል?

የሚገምቱንን ያህል ጠንካራ አለመሆናችንን ከኛ ሌላ ማን ያውቃል? ድኩም የነፍስያችን ገፅስ ለማን ተገልጧል?

ለእግዜር ምኖቹ ነን? ልጆቹ? አምሳሎቹ? ወይስ አንዳች ሌላ አይነት ማንነት አለን? እኛን ከሰው መሀል መርጦ ከምን ከምን አበጀን? አንዳች የጨመረብን ልዩ አክሻፊ ውህድ ላለመኖሩ ምን ማስረጃ አለን?

ዱኩምነታችንን አምነን ተቀብለን ያለመቻሎቻችን ደንገጡሮች ሆነናል።
የምንወዳቸውን ሰዎች ጉንጭ እየሳምን መውደዳችንን ብንነግራቸው እንወድ ነበር - ግን አንችልም!

እምባ ያቀረሩ ዐይኖችን ስናይ ተጠግተን ማፅናናት ያሰኘናል - ግን አንችልም!

"አልችልም" በየማለዳው የምንደግመው ዳዊት ሆኖልናል።

በሰዎች ዐይን የማንሞላ ደቂቅ ፍጥረታት እንደሆንን ለራሳችን ነግረናል። ቀና ብሎ መራመድ ነውር ይመስለናል።

ገና ሳንሞት መቃብራችንን በቀጭን ስንጥር እየጫርን መማስ ጀምረናል። ይህስ ከቅጣቶች ሁሉ የላቀው ቅጣት አይደለምን? ትንሽ ትንሽ ሞቶችን ዕለት ዕለት እንጎነጫለን።

መክሊታችንን በጭቃ ለውሰናል። ህብስታችንን ለውሾች ሰጥተናል። ወርቃችንን በመዳብ ለውጠናል። እንደውሻ ወደትፋትን በመመለስ አዙሪት ውስጥ ወድቀናል። እንደእሪያ ጭቃ ላይ መንደባለል የሰርክ ግብራችን ነው። ለክብር ሳይሆን ለውርደት፤ ለወርቅ ሳይሆን ለመዳብ የተገባን ሰዎች ነን ብለናልና!

መወደድ አንችልበትም። ሰዎች የዋሉልን ኢምንት ውለታ ከቋጥኝ ይልቅ ትከብደናለች። 'መልካም ነገር ሁሉ ለእኛ አይገባንም' ብለን በማመን በአንድያ ራሳችን ላይ እስክንጨክን ድረስ ራሳችንን እንዲሁ ጠልተናልና!

የምናብ ዓለም ሰዎች ነን። መሆን የምንፈልገውን ተቀምተናል። የማንን ኑሮ ይሆን አሁን እየኖርን ያለነው?

ጣታችን እንጂ ምላሳችን ትብ አይደለም። አንደበታችን በአንዳች በማይታይ ልጓም ተሸብቧል። ሰላላ ድምጻችን ለማንስ ይሰማል? "ዝምታችንን ያልሰማ ቃላችንን ሊሰማ አይገባውም" በሚሉት ስንኩል ብሂል ራሳችንን ብናፅናናም ንግግራችንም ከዝምታችን እንዳይለይ ሆኖ በባዶነት ተለብጧል።

ልዝብ ነን፤ ተሰብረን እንኳን ልክ እንደ ብርጭቆ ቆዳ የምንሸረክትበት ስለት የለንም። "ተዉን!" አንልም። ከወጊያችን ጋር ተደርበን ራሳችንን እናጠቃለን።

ልበሙሉነት ይጎድለናል። We are Cowards! ማንንም አንጋፈጥም። ዐይናችን ከዐይኖች ሲገጣጠሙ በቅፅበት እንሰብራቸዋለን። አንደበታችን ከእሺታ ሌላ አታውቅም። ትናጋችን ለእምቢታ ሩቅ ናት። ይሉኝታ ይሉት ጌታ ጨቁኖ የሚገዛን ባሪያዎቹ ነን።


ምን አይነት ድብርታሞች ኖረናል?! ይህ ፍዝ ኑሯችን ሰነፍ ጸሐፊ ከቀመረው ከአንድ አሰልቺ ድንቃይ ተውኔት በምን ይለያል? ተመልካቹ ሁሉ የጀመረውን ተውኔት ሳይጨርስ እያዛጋ ይወጣል። በመጨረሻም ተዋናዩ ብቻውን ይቀራል። እሱ ግን ፀንቶ ትወናውን ይቀጥላል። ይህ ያስመሰግነዋል ወይስ ያስወቅሰዋል?

We are boring!
Aren't we?

[Yeah, the dude in the photo is me ]
451 views00:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 21:28:13
512 views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ